reporter issue 1201

36

Click here to load reader

Upload: heynock

Post on 27-Apr-2015

185 views

Category:

Documents


9 download

TRANSCRIPT

Page 1: Reporter Issue 1201

|ገጽ 1 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRITነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ

ጥቅምት 22 ቀን 2004

የረቡዕ እትም

ቅፅ 17 ቁጥር 8/ 1201 | አዲስ አበባ ኢትዮጵያ | ጳጉሜን 6 ቀን 1987 ተመሠረተ |ዋጋ ብር 7.00

በውስጥ

ገጽ 2

የቢሮክራሲው ዋናው ችግር ምንድን ነው?

አቅም ማነስ? ሙስና? ክፋትና አሻጥር?

ወደ ገጽ ዞሯል4 አቶ ከፍያለው አዘዘ

አቶ ያረጋል አይሸሹም ተከሰሱበ10 ሺሕ ካሬ ሜትር ቦታ በ8.2 ሚሊዮን ብር ንብረት

በባንክ በተቀመጠ ከ490 ሺሕ በላይ ብር በሁለት ተጨማሪ ቦታዎች

የሊዝ አዋጁና የይዞታ ባለቤትነት

በውድነህ ዘነበ

የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ‹‹ልማታዊ የታክስ አስተዳደር ሠራዊት›› ሊፈጥር መሆኑን አስታወቀ:: ባለሥልጣኑ ወደ ሕዝብ በጥልቀት በመግባት በይበልጥ ታክስ መሰብሰብ ያስችላል ያለውን የታክስ አስተዳደር ሠራዊት መፍጠርያ ሰነድ ማዘጋጀቱ ታውቋል:: በዛሬ ዕለት ደግሞ 400 የሚሆኑ የመሥርያ ቤቱ አመራሮች በዚህ ጉዳይ ላይ ሥልጠና ይጀምራሉ::

ባለሥልጣኑ ለሪፖርተር እንደገለጸው፣ ልማታዊ የታክስ አስተዳደር ሠራዊትን ለመፍጠር፣ ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት አራት ቀናት 400 የመሥርያ ቤቱ አመራሮች

ሊፈጥር ነው

‹‹ልማታዊ የታክስ አስተዳደር ሠራዊት››

ገቢዎች ባለሥልጣን

ወደ ገጽ ዞሯል4 አቶ ያረጋል አይሸሹም

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/ናሆ

ም ተ

ስፋዬ

በታምሩ ጽጌ

የፌዴራል የኅብረት ሥራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር፣ የተወካዮች ምክር ቤት አባልና የቀድሞ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ያረጋል አይሸሹም ከ10 ሺሕ ካሬ ሜትር በላይ ቦታ፣ ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ንብረት፣ በባንክ በተቀመጠ ከ490 ሺሕ ብር በላይና በሁለት ተጨማሪ ቦታዎችን በራሳቸው፣ በባለቤታቸውና ለአቅመ አዳም ባልደረሱ ልጆቻቸው ስም ይዘው በመገኘታቸው፣ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት በመያዝ የሙስና ወንጀል በትናንትናው ዕለት ክስ ተመሠረተባቸው::

ከአቶ ያረጋል አይሸሹም ጋር በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት አፈ ጉባዔ አቶ ሀብታሙ ሂካ፣ የጌዲዮን ደመቀ አማካሪ ድርጅት ባለቤትና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌዲዮን ደመቀ፣ በግል ሥራ የሚተዳደሩት አቶ አሰፋ ገበየሁ፣ የጋድ ኮንስትራክሽን ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ አድገህ፣ የኮላን ኮንስትራክሽን ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መክብብ ሞገስና በንግድ ሥራ የሚተዳደሩት አቶ ኃይለ ገብርኤል ሂካ ናቸው::

በተከሳሾቹ ላይ ስድስት ክሶች የቀረቡባቸው ሲሆን፣ አቶ ያረጋል በአምስቱ ሲከሰሱ፣ አቶ ሀብታሙ አራት ክሶች ቀርቦባቸዋል::

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በአቶ ያረጋል፣ በአቶ ሀብታሙ፣ በአቶ ጌዲዮንና በአቶ አሰፋ ላይ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው ክስ እንደሚያስረዳው፣ ግለሰቦቹ ርዕሰ መስተዳድር፣ በወቅቱ የክልሉ ትምህርት

ቢሮ ኃላፊ፣ የአማካሪ ድርጅት ባለቤትና ዋና ሥራ አስኪያጅና የኮንስትራክሽንና ዲዛይን አክሲዮን ማኅበር የዲዛይን ስቱዲዮ ክፍል ኃላፊ ሆነው ይሠሩ ነበር:: ሕገወጥ ጥቅም ለማግኘት በመመሳጠርና በመንግሥት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ፣ የግልገል በለስ መምህራን ኮሌጅ፣ የጣና በለስ የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤትና የአሶሳ ቴክኒክና ሙያ ማሠልጠኛ ተቋምን ለመገንባት ከፌዴራል መንግሥት የተሰጠን የበጀት ድጐማ፣ ሥልጣናቸውን አላግባብ በጠቀም የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል::

ግንባታውን ለማከናወን የጨረታና የግዢ መመርያን የተከተለ መሆን ሲገባው፣ እንዲሁም ከ300,000 ብር በላይ የሚፈጸም የአገር ውስጥ ግዢ በክልሉ ፋይናንስ ቢሮ መጽደቅ

የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር መስከረም 30 ቀን 2004 ዓ.ም. የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ዙርያ

ትናንት ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል:: መግለጫውን የሰጡት ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ደሳለኝ አምባውና በሚኒስቴሩ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እስራኤል ተስፋዬ ናቸው:: አዋጁን በተመለከተ በተለይ

አቶ እስራኤል ለጋዜጠኞች ከሰጡት ማብራርያ የተወሰነውን በገጽ 5

ላይ ይመልከቱ::

አቶ እስራኤል ተስፋዬ

Page 2: Reporter Issue 1201

አድራሻ፡- ቦሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 03 የቤት ቁጥር 2347 ፖስታ 7023 አ.አ ኢትዮጵያ

ማስታወቂያ ሽያጭና ስርጭት 0910 885206/ 011 6 61 61 79/ 85

[email protected] E-mail: [email protected]

Website: www.ethiopianreporter.com

ዋና ሥራ አስኪያጅ፡ አማረ አረጋዊዋና አዘጋጅ፡ መላኩ ደምሴአራዳ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 13/14 የቤት ቁ. 481ምክትል ዋና አዘጋጅ፡ ዘካሪያስ ስንታየሁከፍተኛ አዘጋጅ፡ ዳዊት ታዬ አዘጋጆች፡ ሔኖክ ያሬድ ጌታቸው ንጋቱ

ምሕረት ሞገስ ኃይሌ ሙሉ

ረዳት አዘጋጆች፡ ታደሰ ገ/ማርያም ምሕረት አስቻለው ታምሩ ጽጌ የማነ ናግሽ

ዋና ግራፊክ ዲዛይነር፡ ይበቃል ጌታሁንከፍተኛ ግራፊክ ዲዛይነር፡ ቴዎድሮስ ክብካብግራፊክ ዲዛይነሮች፡ ፀሐይ ታደሰ ፋሲካ ባልቻ እንዳለ ሰሎሞን ስሜነህ ሲሳይ ቢኒያም ግርማ ነፃነት ያዕቆብ ቤዛዬ ቴዎድሮስ

ዋና ፎቶ ግራፈር ናሆም ተሰፋዬፎቶ ግራፈሮች፡ ታምራት ጌታቸው መስፍን ሰሎሞን

ካርቱኒስት፡ ኤልያስ አረዳ

በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር (ኤም.ሲ.ሲ) ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር

እየታተመ የሚወጣ ጋዜጣ

ረቡዕ ጥቅምት 22 ቀን 2004

በጳጉሜን 6 1987 ተጀመረ በሳምንት ሁለት ጊዜ የሚታተም አድራሻ ስልክ 0910-885206/ 011-661 61 79/85/87 ፋክስ: 011-661 61 89

ርእሰ አንቀጽ

ከፍተኛ ሪፖርተሮች፡ ደረጀ ጠገናው ብርሃኑ ፈቃደሪፖርተሮች፡ ብርቱካን ፈንታ ምዕራፍ ብርሃኔማርኬቲንግ ማናጀር፡ እንዳልካቸው ይማምሴልስ፡ ቤዛዊት ፀጋዬ' Hና Ó`T' w\¡ S<K<Ñ@�' IK=ና ከuደማስታወቂያ ፕሩፍሪደር፡መሳይ ሰይፉ፤ ብሩክ ቸርነት፤ ኤፍሬም ገ/መስቀልኮምፒውተር ጽሑፍ፡ ብርቱካን አባተ፣ ሄለን ይታየው፣ አፀደ ካሳዬ፣ ፍሬሕይወት ተሰማሕትመት ክትትል፡ ተስፋዬ መንገሻ፣ የየሱስወርቅ ማሞ፣ ገዛኸኝ ማንደፍሮዌብ ሳይት፡ ቤዛዊት ተስፋዬ፣ ቢኒያም ሐይሉ

የቢሮክራሲው ዋናው ችግር ምንድን ነው?አቅም ማነስ? ሙስና? ክፋትና አሻጥር?ሕዝብ የሚመኘውንና የሚፈልገውን አለማግኘቱ ይቅርና መንግሥት ራሱ የሚፈልገውንና

ለማግኘት የሚጥረውን እንኳ በቢሮክራሲው ምክንያት ማሳካት አልቻለም:: አልተቻለም:: ቢሮክራሲው በበርካታ የውስጥ ችግሮች የተተበተበ ሆኗልና::

ምንጊዜም ቢሆን ቢሮክራሲውን ሙሉ በሙሉ ንፁህና ብቁ ሆኖ ማግኘት አይቻልም:: በእኛ አገርም፣ በሌላ አገርም፣ የበለፀጉና ያደጉ በሚባሉትም::

በእኛ አገር ደግሞ አገራቸውንና ሕዝባቸውን በቅንነት ማገልገል የሚፈልጉ ባለሥልጣናትና ሹመኞች ወይም ሠራተኞች የሉም ማለት አይደለም:: አሉ:: ለማገልገልም፣ ለመለወጥም ፍትሕና ልማትን እውን ለማድረግም የሚጥሩ አሉ:: ነገር ግን የበላይነት የያዘው የቢሮክራሲው ይዘቱና ገጽታው ጉዳዮችን ማጓተት፣ ማደናቀፍ፣ ማበላሸት፣ ቅሬታና ምሬት ማስከተልና ሕዝብና መንግሥትን ማራራቅ ሆኗል::

ችግሩ ምንድን ነው?የቢሮክራሲው ችግሮች ይዘርዘሩ ቢባሉ እጅግ በርካታ ናቸው:: አቅም ማነስ፣ ሙስና፣

ክፋትና አሻጥር እየተባሉ ሊዘረዘሩ ይችላሉ:: እነዚህም በውስጣቸው የተለያዩ ፍረጃዎችና ይዘቶች አሉዋቸው::

የአቅም ማነስ ከፍተኛ ችግር አለ:: በኃላፊነትና በሠራተኛነት የሚመደቡ ሰዎች ከሥራው ጋር የሚመጣጠን የተሟላ እውቀትና ችሎታ የላቸውም ብቻ ሳይሆን፣ አንዳንዶቹ ለተሾሙበት ኃላፊነትና ለተመደቡበት ሥራ ለምን እንደተቀመጡ ግራ ሲገባቸው ይታያሉ:: በሌላ ቦታ የተሻለ ሊሠራ የሚችለው ያለቦታው ተመድቦ ሥራና ምደባ የማይገናኙበት ሁኔታ በመፈጠሩ ችግሮች በግልጽ እየተስተዋሉ ነው::

አንዳንዱ በጭራሽ ለኃላፊነት ብቁ አይደለም:: አንዳንዱ ይበልጥ በአጥቂነት አስተዋፅኦ ሊያደርግ እየቻለ ለምን ግብ ጠባቂ እንደተደረገ ግራ ያጋባል:: ዶክተሩ ሲዘፍን ዘፋኙ ቀዶ ጥገና ሲያደርግ የሚታይበት ሁኔታም አለ:: ሥራና ሠራተኛ፣ ኃላፊነትና ኃላፊ ባለመገናኘታቸው የአቅም ብቃት እውን አልሆነም:: መንግሥትም ሥራውን በአግባቡና በፍጥነት እያከናወነ አይደለም:: ሕዝብም አገልግሎቱን እያገኘ አይደለም::

ችግሩ ግን የአቅም ማነስ ብቻ አይደለም:: ሙስናም አደገኛ በሽታና እንቅፋት ሆኗል:: የእግር ኳስ ፌዴሬሽንና የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተዳክመዋል በምንልበት ወቅት፣ በእጅጉ እየተጠናከረ የመጣው ሕጋዊ ያልሆነ ፌዴሬሽን ‹‹የሙስና ፌዴሬሽን›› ነው::

የቢሮክራሲው የጥበብ መጀመርያ ሙስና እየሆነ ነው:: ሕዝብ አገልግሎት ማግኘት መብቱ ነው የሚለው አስተሳሰብ እየጠፋ ነው:: ደመወዝ የሚገኘው ሕዝብ በሚከፍለው ግብር ነው ማለትም እየተሻረ ነው:: ‹‹ጉቦ የከፈለ አገልግሎት ያገኛል›› ብቻ ሳይሆን፣ ‹‹ቀድሞ ጉቦ የሰጠ ቀድሞ ይገለገላል›› የሚልም ሆኗል:: እሱ ብቻም አይደለም:: ‹‹ይበልጥ የሰጠ ይበልጥ ይገለገላል›› የሚል እያበበና እየደመቀ የመጣ መፈክር ሆኗል:: በከተማም በገጠርም፤ በክልልም በፌዴራልም፤ በላይም በታችም::

ከአቅም ማነስና ከሙስና ውጤት በተጨማሪ በቢሮክራሲው ውስጥ ሌላ ችግር አይታይም? ይታያል እንጂ! ክፋትና አሻጥርም ነግሷል::

የአቅም ችግር አይደለም:: ለጥቅማ ጥቅምና ለሙስና ተብሎም አይደለም:: የፖለቲካ ዓላማ ያለው ችግርም በቢሮክራሲው ውስጥ ይታያል:: የሚቃወመውን መንግሥት በትጥቅ ትግል ወይም በምርጫ ማሸነፍና መጣል ሲያስቸግር ውስጥ ሰርጎ በመግባት ሕዝብና መንግሥት እንዲጣሉ ማድረግም አዲሱ ዘዴ እየሆነ ነው:: የትግል ስልትም ሆኗል::

ሁሉም ተቃዋሚ እንደዚያ ያደርጋል ማለታችን አይደለም:: የማያደርጉ አሉ:: ለአንዳንዶቹ ደግሞ የትግል ‘ስታንዳርድና’ ስልት እየሆነ ነው:: ሆን ብሎ ሕዝብን አለማገልገል፣ ሆን ብሎ ሕዝብ በመንግሥት ላይ እንዲያማርር ማድረግ::

ይህ ችግር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየጐላ የመጣ ነው:: አንዳንዱ ፖለቲከኛ እንደ ወሳኝ የትግል መንገድ ወስዶታል ብቻ ሳይሆን፣ ኢሕአዴግ ራሱም አባላትን ማብዛት በሚል ሰበብና ፈሊጥ በሩን በርግዶ ለአደጋ እየተጋለጠ ነው:: በሰዶ ማሳደድ የሚፈታም አይሆንም::

ከፍ ብለን የዘረዘርናቸው ችግሮች ተግባር ላይ ሲውሉ የተለያዩ አልባሳትን ይለብሳሉ:: አቅም ማነስ፣ ሙስና፣ ሸርና ክፋት ተግባር ላይ ሲውሉ የዘር፣ የጐሳ፣ የሃይማኖት፣ የቤተሰብነት፣ የጓደኝነትና የልዩ መቀራረብ ሽፋንም ይደረግባቸዋል:: ይህም በግልጽ በቢሮክራሲው ውስጥ እየታየ ነው::

እነዚህ በቢሮክራሲው ላይ እየታዩ ያሉ ችግሮች ኅብረተሰቡን እየጐዱ ናቸው:: ፍትሕን፣ ዲሞክራሲንና ልማትን እያደናቀፉ ይገኛሉ:: ሕዝቡ በኢትዮጵያዊነቱ እንዲሠራ ከማድረግ ይልቅ ተስፋ እያስቆረጡና እያሸማቀቁ ያሉት ችግሮች፣ ወቅታዊና እየተጠናከሩ በመቀጠል ላይ ያሉ ናቸው::

ቢሮክራሲው የመንግሥት መዋቅርና አካል ቢሆንም ለችግሮቹ ግን የኅብረተሰቡ ድርሻም አለበት:: ፍላጐቴ እስከተሳካልኝ ድረስ ጉቦ እሰጣለሁ፤ ተንኮልም ልፈጽም፣ በድንቁርና ልገልገልም ችግር የለም የሚል ኅብረተሰብ፣ ችግሩን ለመፍታት ከማገዝ ይልቅ ለማባባስ አስተዋፅኦ ይኖረዋል:: ለጉቦ ተቀባይ ዋስትናው ጉቦ ሰጪ መሆኑ ግልጽ ነው::

ችግሩን ለመፍታትና ለማስተካከል ልዩ ኃላፊነትን የሚሸከመው ግን መንግሥት ይሆናል:: መንግሥት የራሱን ቢሮክራሲ ማጥራትና ማስተካከል አለበት:: ችግሮቹን ለይቶ ማወቅ አለበት:: ዋነኛው ችግር ምንድን ነው? ተያይዞና ተሳስሮ የሚከተለው ችግርና እንቅፋት ምንድነው? ብሎ ለይቶ ማወቅ ይኖርበታል::

ቢሮክራሲውን ለማጠናከር በሚል መንግሥት ኃላፊዎችን እያሠለጠነ ይገኛል:: ሥልጠናውን በተከታታይ እያደረገውም ነው:: አቅም ለሌለው በሥልጠና አቅም መጨመር ይቻላል:: ሙሰኛውን ግን በሥልጠና ባህርይውን መለወጥ ያስቸግራል:: ሆን ብሎ ውስጥ ገብቶ የሚቦረቡረውን በሥልጠና አቋሙን መቀየር በጣም በጣም ይከብዳል::

ስለሆነም ችግርን ለይቶ ማወቅና የሚሠለጥነውን አሠልጥኖ፣ የሚባረረውን አባሮ፣ ሕዝብን የሚያገለግል መዋቅር መዘርጋት አንገብጋቢና የወቅቱ ጥያቄ ነው:: የሕዝብ ጥያቄ!

Page 3: Reporter Issue 1201

|ገጽ 3 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

በውድነህ ዘነበ

በግብርና ሥራ ላይ የተሰማራው የህንዱ ግዙፍ ኩባንያ ካሩቱሪ በተረከበው መሬት ላይ የህንድ ገበሬዎችን የማስፈር ዕቅድ እንደሌለው አስተባበለ:: ኩባንያው በግብርና ሚኒስቴር በኩል ለሪፖርተር በላከው ደብዳቤ የተረከበውን መሬት በራሱ እንደሚያለማው ገልጿል::

ከጥቂት ሳምንታት በፊት የካሩቱሪ አንድ የሥራ ኃላፊ የህንድ ገበሬዎችን በኢትዮጵያ የእርሻ ሥራ ለማሠራት ማቀዳቸውን ለህንዱ

ቢዝነስ ስታንዳርድ ገልጸው ነበር:: መግለጫውን ተከትሎ ሪፖርተርን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኅን ሲዘግቡ ቆይተዋል::

ኩባንያው ባለፈው ረቡዕ በላከው ደብዳቤ፣ የህንድ ገበሬዎችን በኢትዮጵያ ለማስፈር የታቀደ ዕቅድ አለመኖሩን አስተባብሏል:: ካሩቱሪ በጋምቤላ ክልል 100 ሺሕ ሔክታር መሬት ተረክቧል:: በዚህ መሬት ላይ ሩዝ፣ ጥጥ፣ የፓልም ዘይትና የሸንኮራ አገዳ ልማት የማካሄድ ዕቅድ አለው::

የካሩቱሪ ኃላፊ በወቅቱ እንደገለጹት፣ ከ100 ሺሕ ሔክታር መሬት ላይ 20 ሺሕ ሔክታር

ቀንሰው የህንድ ገበሬዎችን በማስፈር ከሚገኘው ጥቅም 65 በመቶ ካሩቱሪ፣ 35 በመቶ የህንድ ገበሬዎች ተካፋይ ይሆናሉ::

የግብርና ሚኒስቴር የኢንቨስትመንት ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኢሳያስ ከበደ ከአንድ ሳምንት በፊት ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ መንግሥት መሬቱን የሰጠው ለኩባንያው ነው:: ማልማትም ያለበት ራሱ ኩባንያው ነው:: ካሩቱሪ የተሰጠውን መሬት ለህንድ ገበሬዎች ቢያከፋፍል፣ መንግሥት ወዲያውኑ እንደሚነጥቀው መግለጻቸው ይታወሳል::

በየማነ ናግሽ

የዓረና ትግራይ ምክትል ፕሬዚዳንት የአቶ ብርሃኑ በርሃ ጽሕፈት ቤት መዘረፉን ፓርቲው ገለጸ:: ጽሕፈት ቤቱ ውስጥ የተገኙ የፓርቲው መረጃዎችና የፖለቲካ ሰነዶች የያዙ ኮምፒውተሮች፣ ፕሪንተሮችና ጥናቶች መዘረፋቸውንና ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፓርቲው አስታውቋል::

የዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉዓላዊነት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት አብርሃም፣ በመቀሌ ከተማ ደቡብ ወረዳ ቀዳማይ ወያነ (ቀበሌ 16) አካባቢ የሚገኘው የአቶ ብርሃኑ ጽሕፈት ቤት የተዘረፈው ከትናንት በስቲያ ሌሊት ሲሆን፣ የተዘረፉ ንብረቶችም የፓርቲው ፋይሎች፣ ሰነዶችና ጥናቶች ስለሚገኙበት በክልሉ መንግሥት የተቀነባበረ ሳይሆን እንዳልቀረ ገልጸዋል::

ጽሕፈት ቤታቸው የተዘረፈባቸው አቶ ብርሃኑ በርሃ በበኩላቸው፣ ስርቆቱ የተካሄደው በተመሳሳይ ቁልፍ መሆኑንና የአከራያቸው እጅ ሳይኖርበት እንደማይቀር ጥርጣሬያቸውን ለሪፖርተር አስረድተዋል:: ላለፉት ሦስት ወራት የፓርቲውን ሥራ ለመሥራት በአሜሪካ ቆይታ ያደረጉት አቶ ብርሃኑ፣ ፓርቲው ቢሮውን ከተከራየው ገና ሁለት ሳምንት ነው ብለዋል:: አካባቢው የኤሌክትሪክ ብርሃን ያለበትና የቀበሌ ጥበቃ አባላት የሚገኙበት በመሆኑ ያለ ምንም ከለላ ስርቆቱ ሊፈጸም እንደማይችል ይናገራሉ::

ቢሮው አዲስ ቁልፍ እንዲቀየርለት የተጠየቁት አከራይ ለሁለት ሳምንታት ሙሉ ዝም በማለታቸው ከጉዳዩ ጋር ሊያያዙ ይችላሉ ብለዋል::

የፓርቲው አንዳንድ ወሳኝ ፋይሎችና ከ189 ገጽ በላይ የሆነው በቅርቡ በመጽሐፍ መልክ ለሕትመት ለማብቃት ያዘጋጁዋቸው ‹‹አብዮታዊ

ዴሞክራሲ ተጠየቅ››፣ ‹‹ሚስጥረ ተሀድሶ በመልካም አስተዳደር›› (151 ገጽ) እንዲሁም ‹‹Good Governance›› (129 ገጽ) የተሰኙ ጽሑፎችን የያዘ የኮምፒውተር ፕሮሰሰርና ፕሪንተር መሰረቃቸውን አቶ ብርሃኑ ይገልጻሉ:: እርሳቸው እንደሚሉት የፓርቲ ስብሰባዎች የተቀረጹባቸው ሲዲዎችም ተሰርቀዋል::

የአካባቢው ቀዳማይ ወያነ ፖሊስ ጣቢያ ምክትል ሳጅን አዳነ ሀብቶም፣ ጽሕፈት ቤቱ የተሰረቀው በተመሳሳይ ቁልፍ መሆኑን ለሪፖርተር ያረጋገጡ ሲሆን፣ የቢሮው አከራይና የበሩን ቁልፍ የሠራ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል::

የአካባቢው ፖሊስ ጉዳዩን በማጣራት ላይ የሚገኝ መሆኑን ገልጸው፣ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ከመናገር ተቆጥበዋል::

የዓረና ምክትል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ተዘረፈ

የፓርቲው የፖለቲካ ሰነዶችና ጥናቶች ተወስደዋል በታምሩ ጽጌ

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ በተመሠረተባቸው ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞችና ሁለት የኦብነግ ታጣቂዎች ላይ፣ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በትናንትናው ዕለት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሦስተኛ ወንጀል ችሎት ምስክሮቹን አሰማ::

የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) ታጣቂ በነበሩት አብዲወሊ መሐመድና ከሊፍ ዓሊ ዳሂር፣ እንዲሁም ኦብነግን ለመደገፍ በውጊያ ላይ ሲሳተፉ ተማረኩ የተባሉት የስዊድን ጋዜጠኞች፣ ጋዜጠኛ መርቲን ካርል ሽብዬና ፎቶ ጋዜጠኛው ጁሃን ካርል ፐርሰን ላይ ዓቃቤ ሕግ ያቀረባቸው አራት ምስክሮች ናቸው::

የዓቃቤ ሕግ የመጀመሪያ ምስክር ሆነው የቀረቡት ተጠርጣሪዎቹን፣ በተለይ ሁለቱን የስዊድን ጋዜጠኞችን በቁጥጥር ሥር ያዋለውን የሶማሊያ ልዩ የፖሊስ ሠራዊት ይመሩ የነበሩት ኢንስፔክተር መሐመድ ሙሐመድ ናቸው:: ኢንስፔክሩ በምስክርነት ቃላቸው እንደገለጹት፣ አብዲወሊ መሐመድና ከሊፍ ዓሊ አሌና አዋሬ በሚባሉ የሶማሌ ክልል ሁለቱን የስዊድን ጋዜጠኞች ጨምሮ በአካባቢው መታየታቸውን ከአካባቢው ነዋሪዎች ጥቆማ ይደርሳቸዋል:: በጥቆማው መሠረት ክትትል ሲያደርጉ በሰኔ ወር ትክክለኛ ቀኑ በማይታወቅበት አንድ ቀን ከሌሊቱ 7 ሰዓት ላይ 11 አሸባሪዎችን የጫነ ተሽከርካሪ በሦስት ኪሎ ሜትር ላይ ታየ:: ከመንግሥት ወታደሮችም በኩል ሌላ ተሽከርካሪ ስለነበርና መብራቱ በመታየቱ የአሸባሪዎቹ ተሽከርካሪ ወደኋላ ተመለሰ:: የተሽከርካሪውን ወደኋላ መመለስ የተመለከተው የሶማሊያ ልዩ ፖሊስ በመከታተል ሊደርስበት ሲል፣ ሾፌሩ ተሽከርካሪውን አቁሞ በመውረድ አቃጥሎት መሰወሩን ምስክሩ በፍርድ ቤት አስረድተዋል::

የኦብነግ ታጣቂዎችን ዙሪያውን የከበበው ልዩ ፖሊስ ውጊያ በመግጠም የተወሰኑት ታጣቂዎችን በመግደል፣ ጋዜጠኞቹ ሳይገደሉ እንዲያዙ ምስክሩ ባስተላለፉት ትዕዛዝ፣ በኦብነግ ታጣቂዎች

በተተኮሰ ጥይት እጃቸውን ብቻ ቆስለው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስረድተዋል:: ከሁለቱ የኦብነግ ታጣቂዎች ከሊፍ ዓሊ የሚባለው የመንግሥት ሠራተኛ እንደነበርና እንደሚያውቁት የተናገሩት ምስክሩ፣ አብዲወሊን ጨምሮ በውጊያ ላይ መማረካቸውን አስረድተዋል::

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት 90 ኪሎ ሜትር ያህል ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ዘልቀው ገብተው መሆኑን የገለጹት ምስክሩ፣ ጋዜጠኞቹ በኦብነግ ታጣቂዎች የተመቱት ሚስጥር እንዳያወጡ ለመግደል እንደነበር ጠቁመዋል:: በቁጥጥር ሥር ሲውሉም የተለያዩ ሁለት ካሜራዎች፣ ሞባይል፣ ላፕቶፕና ሌሎችንም ሰነዶች ማግኘታቸውን ተናግረዋል::

የኦብነግ ታጣቂዎች ለነበሩት የሶማሌ ተወላጆች የቆሙት ተከላካይ ጠበቃ ሳሙኤል አባተ፣ በምን ያህል ርቀት ላይ እንደተገናኙ ምስክሩን ሲጠይቋቸው በመቶ ሜትር ርቀት ላይ ሆነው ተኩስ መጀመራቸውን ተናግረዋል::

ለጋዜጠኞቹ ጠበቃ ሆነው የቀረቡት አቶ አበበ ባልቻ፣ አቶ ስለሺ ቀፀላና አቶ ደርበው ተመስገን ሲሆኑ፣ አቶ ስለሺ ለዓቃቤ ሕግ ምስክር “ለምን እንዳያችኋቸው አልያዛችኋቸውም? በምን ያህል ርቀት ላይ ሆናችሁ ነው ታጣዎቂች መኖራቸውን ያረጋገጣችሁት?” የሚሉ ጥያቄዎችን አንስተውላቸው፣ የያዟቸው በውጊያ ውስጥ መሆኑንና ያዩአቸውም በአጉሊ መነፅር መሆኑን በመግለጽ ምላሽ ሰጥተዋል::

ሙሉ ቀን የፈጀው የዓቃቤ ሕግ የምስክርነት ቃል በይደር ለዛሬ የተቀጠረ ሲሆን፣ በትናንትናው ዕለት ከሰዓት በኋላ ከሶማሌ ክልል የመጡ አሥር አለቃ ዴግ አብዲ ከመጀመሪያው ምስክር ጋር ተመሳሳይነት ያለው የምስክርነት ቃል ሰጥተዋል:: ሦስተኛና አራተኛ የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች ከአዲስ አበባ ሲሆኑ፣ የምስክርነት ቃላቸውም ተከሳሾቹ በምርመራ ወቅት በፍላጐትና በነፃነት ቃላቸውን የሰጡ መሆናቸውን የሚመሰክሩ ናቸው:: ፍርድ ቤቱ የዓቃቤ ሕግን የኦዲዮና የቪዲዮ ማስረጃዎችን ለማየትና ለማዳመጥና ለመመልከት ለዛሬ በይደር ቀጥሯል::

በሽብር ወንጀል በተከሰሱት የስዊድን ጋዜጠኞች ላይ ምስክርነት ተሰማ

• “በጥይት ተመተው የቆሰሉት በኦብነግ ታጣቂዎች ነው” የዓቃቤ ሕግ ምስክር

ካሩቱሪ የህንድ ገበሬዎችን የማስፈር ዕቅድ የለኝም አለ

Page 4: Reporter Issue 1201

ገጽ 4|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

VACANCYThe International Institute of Rural Reconstruction (IIRR) is an international development, research and training organization with over 90 years of grass-root experience working in Africa, Asia and Latin America. Since 1920, IIRR has been building the capacity of the poor and their organizations to help them address the root causes of poverty and to help them develop and deliver sustainable solutions. Jointly with grass-root partners, IIRR undertakes participatory action research where various poverty reduction approaches and technologies are tested, lessons and best practices documented through practice based trainings, workshops, study missions and publications.

IIRR-Ethiopia seeks to recruit an experienced

1. Partnership and Resource Mobilization Specialist

Requirements:

• Postgraduate qualification (MA, PhD) in economics, business, education, or any other relevant social science field.• Experience working in a capacity building work.• At least five years experience in managing multi-year projects in non-governmental organizations.• Excellent proposal writing skills and hands-on experience in fund-raising.• Excellent computer skills – word-processing, excel, PowerPoint, etc.• Facilitation skills.

Salary: NegotiableWork Place: to be based in Addis Ababa with some travel to field

2. Project Officer

Requirements:

• At least a first degree in agriculture, education, or any other relevant social science field.• Experience in initiating and coordinating food security and livelihood programs preferably in pastoralist areas.• Experience working in pastoralist areas is an advantage.• Excellent proposal and report writing skills (in English).• Excellent computer skills – word-processing, excel, PowerPoint, etc.• Women are highly encouraged to apply.• Speaking Oromifa is advantageous

Salary: Negotiable

Work Place: to be based in Addis Ababa with 30% field travel

An application letter with an updated CV should be sent by email to [email protected] . No other document is required at the application phase. Applications will be accepted for seven (7) days from the announcement of this vacancy. The organization shall notify shortlisted candidates, hence applicants do not need to make a follow up.

Vacancy Announcement The Ethiopian Society of Obstetricians and Gynecologists (ESOG), would like to invite competent applicants for a full-time position for the project entitled “Improving Comprehensive Emergency Obstetric and Newborn Care Services in the Regional Hospitals of Ethiopia” in collaboration with the Federal Ministry of Health

Position: Obstetrician and Gynecologist Required number: Five Term of employment: Contractual Duty station: Oromiya, Tigray and Amhara Regions Salary: Negotiable

Responsibilities: Under the supervision of the Project Coordinator /General Manager of ESOG, the Obstetrician and Gynecologist will be responsible for:

1. Providing Comprehensive Emergency Obstetric and Newborn Care and conduct training and assessment on the selected sites.

2. Mentoring trained providers to ensure adequate skill transfer. 3. Overseeing the proper execution of planned activities of the project. 4. Ensuring training reports are prepared, compiled and submitted to the office on

time.5. Representing the Society with regards to the project when delegated by the

General Manager. 6. Availing technical information and training reports in relation to the project to

the office, donors, government bodies and the public at large with the view of improving the image of the Society.

7. Proposing/conducting appropriate researches related to the project whenever necessary.

8. Providing technical assistance to projects and other activities of the Society.

Qualification:

1. M.D, with Specialty in Obstetrics and Gynecology2. Experience of working within the public sector and/or NGO 3. Good interpersonal communication skill and ability to work

harmoniously with colleagues, partners and stakeholders.Interested applicants should submit their application with non-returnable relevant documents in person, by fax or e-mail to the following address within 7 days of this publication.

Ethiopian Society of Obstetricians and Gynecologists (ESOG) P. O. Box 8731Addis Ababa

Tel: 251-115-506 068/69Fax: 251-115-506-070

E-mail: [email protected]

ሥልጠና እንደሚጀምሩ አረጋግጧል:: እነዚህ አመራሮች ሥልጠናቸውን

ካጠናቀቁ በኋላ ባለሥልጣኑ በሰነዱና በታክስ አሰባሰብ ዕቅዱ ዙርያ ከግብር ከፋዩ ኅብረተሰብ ጋር ለመወያየት ማቀዱን አስታውቋል:: የባለሥልጣኑ የትምህርትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኤፍሬም መኮንን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ባለሥልጣኑ በሰነዱ አማካይነት በዘርፉ ላይ የተጋረጡ የተባሉ አደጋዎችን በመለየትና ሙስናን በመታገል ገቢ የመሰብሰብ አቅሙን የማጠናከር ዕቅድ አለው::

ባለሥልጣኑ በአገር አቀፍ ደረጃ ‹‹ልማታዊ የታክስ አስተዳደር ሠራዊት የመፍጠር ዕቅድ አውጥቷል:: በሰነዱ ላይ ለአመራሮች ሥልጠና በመስጠት አጠቃላይ ንቅናቄ የመፍጠር ዕቅድ ነድፏል፤›› ብለዋል::

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በበጀት ዓመቱ ዋዜማ ካፀደቀው 117.8 ቢሊዮን ብር ዓመታዊ በጀት ውስጥ፣ 70 ቢሊዮን ብር የሚሰበሰበው በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን አማካይነት እንደሚሆን መገለጹ ይታወሳል::

ይሁንና ባለሥልጣኑ ቀደም ሲል በራሱ የውስጥ ዕቅድ እሰበስበዋለሁ ብሎ ያቀደው 76 ቢሊዮን ብር ነበር:: ይህንን ገቢ ለመሰብሰብ ባለሥልጣኑ በርካታ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ ሲገልጽም ነበር::

ገቢዎች ... ከገጽ 1 የዞረ አቶ ያረጋል... ከገጽ 1 የዞረ

ሲኖርበት፣ ይህንን በመተላለፍ የተመደበው ገንዘብ ከፍተኛ መሆኑን እያወቁ የተሻሉ ተወዳዳሪዎችን ሳያጫርቱ የሦስቱንም ፕሮጀክቶች ጨረታ በሕገወጥ መንገድ ለጌዴዮን ደመቀ አማካሪ ድርጅት መስጠታቸውን የክስ ቻርጁ ያብራራል::

አቶ ጌዲዮንና አቶ አሰፋ ከዲዛይን ሥራው 250,000 ብር፣ ለቁጥጥርና ለአስተዳደር ከሚከፈለው በየወሩ 10,000 ብር ለአቶ ያረጋልና ለአቶ ሀብታሙ ለመስጠት በሚስጥር በመደራደር የጥቅም ግንኙነት መመሥረታቸውን ክሱ ይገልጻል::

የጥቅም ግንኙነቱን ተግባራዊ ለማድረግ አቶ ያረጋል በነበራቸው ሥልጣን በመጠቀም፣ የሦስቱም ፕሮጀክቶች ጨረታ አቶ ሀብታሙ በሚመሩት ትምህርት ቢሮ ሥር እንዲከናወን በ1998 ዓ.ም. አዘዋል:: የክልሉ የግዢ መመርያ ከሚያዘው ውጭ ሥራው አስቸኳይ ነው በሚል በውስን ጨረታ እንዲከናወን መመርያ አስተላልፈዋል::

አቶ ሀብታሙ ከአቶ ያረጋል የተላለፈላቸውን መመርያ በመከተል፣ ለአቶ ጌዲዮንና ለአቶ አሰፋ የጨረታው ሰነድ ሳይሞላ እንዲላክ በማድረግ፣ ከጨረታ ኮሚቴ የተላከላቸውን የውሳኔ ሐሳብ በማፅደቅ፣ ደረጃው የማይፈቅድለት የጌዲዮን ደመቀ አማካሪ ድርጅት አሸናፊ እንዲሆን ማድረጋቸውንና ቃል የተገባላቸውን 50,000 ብር መቀበላቸውን ክሱ ያስረዳል::

አቶ ሀብታሙ በተጣለባቸው ኃላፊነት መሠረት የመንግሥትንና የሕዝብን ጥቅም ማስጠበቅ ሲገባቸው፣ በ13 ወራት ውስጥ ያልቃል የተባለው ፕሮጀክት ላለፉት አምስት ዓመታት ካለመጠናቀቁም በተጨማሪ፣ ለጌዲዮን ደመቀ አማካሪ ድርጅት በድምሩ 2,832,450 ብር ተጨማሪ ክፍያ እንዲፈጸም ማድረጋቸውን ክሱ ያብራራል::

አቶ ያረጋልና አቶ ሀብታሙ ፕሮጀክቱ እንደማይሠራ እየተረዱ ከአቶ ጌዲዮንና ከአቶ አሰፋ ጋር በመሠረቱት ሕገወጥ የጥቅም ግንኙነት መሠረት፣ ሥራውን በመዋዋልና ከአምስት ዓመት በላይ በማጓተት፣ ከውሉ ውጭ ከፍተኛ ገንዘብ በመውሰድ ሕገወጥ ተጠቃሚ ሆነው በመገኘታቸው በፈጸሙት በሥልጣን አላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ተከሰዋል::

ከአቶ ያረጋል ከአቶ ሀብታሙ፣ ከአቶ ጌዲዮንና ከአቶ አሰፋ ጋር በሁለተኛ ክስ የተከሰሱት የጋድ ኮንስትራክሽን ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ አድገህ፣ በሕገወጥ መንገድ በስውር በመመሳጠር ጥቅም ለማግኘትና በመንግሥት ጥቅም ላይ ጉዳት

ለማድረስ፣ የግልገል በለስ መምህራን ኮሌጅና የጣና በለስ የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት ፕሮጀክትን ከጨረታና መመርያ ውጪ፣ አቶ ያረጋልና አቶ ሀብታሙ እንዲሰጧቸውና ለሥራው መጀመርያ 3,000,000 ብር እንዲሰጧቸው ሕገወጥ ግንኙነት መመሥረታቸውን ክሱ ያስረዳል::

በመሆኑም አቶ ያረጋል ለአቶ ሀብታሙ ባስተላለፉት ትዕዛዝ መሠረት ቀደም ብለው ግንኙነት ከፈጠሩት ከጌዲዮን ደመቀ አማካሪ ድርጅት ጋር በሕገወጥ መንገድ ግንኙነት በመፍጠር፣ የተደረገውን ውስን ጨረታ ጋድ ኮንስትራክሽን እንዲያሸንፍ ተደርጓል:: ጋድ ኮንስትራክሽን፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ጋር የጣና በለስ ሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤትን በ28,502,641.60 ብርና ግልገል በለስ መምህራን ኮሌጅን በ29,981,635.07 ብር እንዲሠራ መዋዋሉን ክሱ ይገልጻል::

እንደ ሌሎቹ ተከሳሾች ሁሉ ሕገወጥ ጥቅም ለማግኘትና በመንግሥት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ፣ የኮላን ኮንስትራክሽን ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መክብብ ሞገስም በሦስተኛው ክስ ውስጥ ክስ ቀርቦባቸዋል:: አቶ መክብብም በሕገወጥ ጨረታ በመሳተፍ የተሻሉ ተወዳዳሪዎች ሳይጋበዙ ተጫርተው፣ የአሶሳ ቴክኒክና ሙያ ማሠልጠኛ ተቋም ግንባታ ሥራን ካሸነፉ ለአቶ ያረጋልና ለአቶ ሀብታሙ 700,000 ብር ሊሰጧቸው በተስማሙት መሠረት፣ የተቋሙን ግንባታ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ጋር 11,229,1265.85 ብር አሸናፊ እንዲሆኑ መደረጋቸውንና ውል መፈጸማቸውን ክሱ ያብራራል:: አቶ ጌዲዮንና አቶ አሰፋ ምንም ዓይነት ሕጋዊ ሥልጣን ወይም ውክልና ሳይኖራቸው በርካታ ስህተቶችን መፈጸማቸውን ክሱ በዝርዝር ይገልጻል:: በመሆኑም ሁሉም ተከሳሾች በፈጸሙት አላግባብ ሥልጣንን የመገልገል ሙስና ወንጀል ተከሰዋል::

አቶ ያረጋል ጥር 30 ቀን 2003 ዓ.ም. በፌዴራል የሥነ

ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በመገኘት ያስመዘገቡት ሀብት በእሳቸውና በባለቤታቸው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግልገል በለስ ቅርንጫፍ ያስቀመጡትን 340,290.68 ብር፣ በግልገል በለስ ከተማ የሚገኝ 1,000 ካሬ ሜትር ቦታ፣ በባለቤታቸው ስም በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ውስጥ በ269 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የተሠራ ቤት፣ መተከል ከተማ ድባጤ ወረዳ ለአቅመ አዳም ባልደረሰ ልጃቸው ስም ያለ 449.87 ካሬ ሜትር ቦታ፣ በሌላኛ ልጃቸው ስም ያለ 1,040 ካሬ ሜትር ቦታ ሲሆን፣ ሳያስመዘግቡ ደብቀውት የተገኘም ቦታ መኖሩን የክስ ዝርዝሩ ያስረዳል::

አቶ ሀብታሙ ሂካ ደግሞ አሶሳ ከተማ 1,031.88 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ የንግድ ድርጅት፣ መተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ 1,200 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሆቴል፣ ወንበራ ወረዳ ደብረ ዘይት ከተማ በ2,400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ የመዋዕለ ሕፃናት፣ በግልገል በለስ ከተማ 500 ካሬ ሜትር ቦታና 391 ካሬ ሜትር ቦታ፣ በወንበራ ወረዳ ደብረ ዘይት ከተማ 50 ካሬ ሜትር ቦታ፣ አሶሳ ከተማ 414 ካሬ ሜትር ቦታ፣ በባለቤታቸው ስም በአሶሳ ከተማ 500 ካሬ ሜትር ቦታ፣ በወንድማቸው ስም በ10 ሚሊዮን ብር የተቋቋመ በጋ አግሮ ኢንዱስትሪና በወንድማቸው ስም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ዩፎሪያ ኢንተርናሽናል ቢዝነስና በ10 ሚሊዮን ብር የተቋቋመ የእምነበረድ ማምረቻ በሚስጥር ይዘው በመገኘታቸው፣ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት በመያዝ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል::

ዓቃቤ ሕግ ዘጠኝ የሰዎችና 63 የሰነድ ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል:: ፍርድ ቤቱ ዓቃቤ ሕግ የቅድመ ክስ መግለጫን ለማድመጥ ለኅዳር 12 ቀን 2004 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል:: በአቶ ኃይለ ገብርኤል ሂካ ላይ የዋስትና መብት ጉዳይ ዓቃቤ ሕግ ተቃውሞ እንደሌለው በመግለጹ፣ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ቀጠሮ ተሰጥቶ ችሎቱ አብቅቷል::

Page 5: Reporter Issue 1201

|ገጽ 5 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

የሊዝ አዋጁና የይዞታ ባለቤትነትበውድነህ ዘነበ

ቀደም ሲል የነበረው አዋጅ 272/94 ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ሥራ ላይ ውሏል:: እንደምታውቁት መሬት የከተሞች ብቸኛ ሀብት ነው:: ይህንን ብቸኛ ሀብት በአግባቡ ለማስተዳደር በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ አዋጆች ወጥተዋል:: የእነዚህ አዋጆች አካል የሆነው አዋጅ ቁጥር 272 በሥራ ላይ በነበረበት ጊዜ አዋጁ ሲወጣ ያላያቸው ከፍተኛ ክፍተቶችና ችግሮች ተከስተዋል:: እንዲሁም መሬትን የተሻለ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲኖረው ለማስቻል የተሻለ አሠራር መፍጠር አስፈልጓል::

ይህ ሥርዓት ካልተፈጠረ በተለይ በከተማ መሬት ላይ ትልቅ ችግርና የኪራይ ሰብሳቢነት አደጋ ነው የሚኖረው:: ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት የታየውን ችግር ለመፍታት በመጀመርያ የዳሰሳ ጥናት ተደርጓል:: ጥናቱ በመሬት ላይ በተጨባጭ ያሉ ችግሮችን የለየ ነው:: ከዚህ ጥናት ተነስተን ወደ ፖሊሲው ነው የገባነው:: የፖሊሲው አቅጣጫ መሬት ላይ ወጥ የሆነ ልማትና ማኔጅመንት እንዲኖር የሚያስችል ነው:: እነዚህን ችግሮች በፖሊሲው ምላሽ ተሰጥቶ ወደ ሕግ አግባብ መጥቷል ማለት ነው:: እንደአብነት ከነበሩት ችግሮች አንዱ ክፍተት፣ መሬት ላይ ምንም ዓይነት ግንባታ ሲያካሂዱ ወይም ከደረጃ በታች የሆነ ግንባታ በማካሄድ ለሦስተኛ ወገን ማስተላለፍ ነው::

ከዚህ ግብይት መንግሥት ሊያገኝ የሚገባው ጥቅም በግለሰቦች ኪስ ውስጥ እንዲገባ ሆኗል:: በዚህ ዘርፍ ትልቅ የኪራይ ሰብሳቢነት አደጋ ነው የተፈጠረው:: ይህ ማለት ባዶ መሬትን፣ ለልማት ሊውል የሚችል መሬትን፣ ወቅት ጠብቆና አጥሮ ይዞ ከዚያ በኋላ በጊዜ ሒደት ምንም ዓይነት እሴት ሳይጨመር በማስተላለፍ ብቻ፣ አላግባብ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ወደተወሰኑ ግለሰቦች ኪስ እየገባ የንብረት ልውውጡን ገበያ አናግቷል::

ሌላው ትንሽ መሠረት ተጥሎና መሠረት የጣለበትን ቦታ በመሸጥ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብም ሲታፈስ ቆይቷል:: ይኼ የራሱ የሆነ ትልቅ ችግር ነው:: ሌላው በዚህ አዋጅ የነበረው አንዱ ከተሞች በጊዜ ሒደት ወደ ሊዝ ሥርዓት ይሸጋገራሉ ይላል:: ሆኖም ግን የአዋጅን መንፈስ ተከትሎ ወደ ሊዝ የማሸጋገር ሒደቱ ከክልል ክልል፣ ከከተሞች ከተሞች ወጣ ገባ ነው የሆነው:: አሁን ባለው ሁኔታ 150 ከተሞች ብቻ ናቸው በሊዝ ሥርዓት መሬት በማስተላለፍ ላይ ያሉት:: ይኼ ማለት በሊዝ ሥርዓት ቦታ ማስተላለፍ ማለትና አሁን ያለውን ነባር ይዞታን ወደ ሊዝ ማስተላለፍ የተለያዩ ነገሮች ናቸው:: በሊዝ አግባብ ቦታ ማስተላለፍ ማለት መንግሥት መሬት ላይ የመሠረተ ልማት አሟልቶ ማስተላለፍ ማለት ነው:: ይኼ እንግዲህ በአገር አቀፍ ደረጃ 950 ከተሞች አሉ:: ከእነዚህ ውስጥ 150 ናቸው ይህንን የሚገለገሉበት:: የሊዝ ሥርዓቱ ካለው ጠቀሜታ አንፃር ወደ ሊዝ ሥሪት ማስገባቱ ዘግይቷል:: ይህንን ማስተካከል አስፈልጓል::

ሌላው የመሬት አሰጣጥ ስልቱ በጣም ወጣ ገባ ነው:: የቀድሞ አዋጅ ከድርድር ጀምሮ አምስት ያህል ቦታ የሚሰጥበት ስልት ነበረው:: እነዚህ ስልቶች ወደታች ሲወርዱ አፈጻጸማቸውም ይለያያል:: ከድርድር ጀምሮ በዕጣ፣ በሽልማት፣ በምደባና በጨረታ ቦታ ሲሰጥ ቆይቷል:: የስልቶቹ አተገባበር የተለያየ ነበር:: ይህንን ሁኔታ ወጥ ማድረግ ያስፈልጋል:: ግልጽ በሆነ መንገድ ስልቱን ማስተካከል ያስፈልጋል:: ከዚህ በመነሳት በአዋጁ ሁሉም ክፍል ላይ ማሻሻያ ተደርጓል:: አንደኛ የመሬት አስተዳደርና ልማት ሥርዓቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲኖር ማስቻል ነው:: በጣም ግልጽ ተጠያቂነት ያለበት አሠራር ለማስፈን አዲሱን አዋጅ ቁጥር 272/2004 ማውጣት አስፈልጓል:: አዋጁ አምስት ክፍሎችንና 37 አንቀጾችን ይዞ ወጥቷል:: በስፋት በመሬት ላይ ትኩረት አድርጎና እንዲስተካከል በሚያደርግ መልኩ ተቀርጿል::

አዋጁ ከፍተኛ ውዥንብርና ስጋት በኅብረተሰቡና በቤተሰብ ውስጥ አምጥቷል

አዋጁ መስከረም 30 ቀን 2004 ዓ.ም. ነው የፀደቀው:: ከዚያ ጊዜ በኋላ በኅብረተሰቡ ውስጥ ለማስረፅ የተወሰነ ጊዜ ወስዷል:: ይኼንን አዋጅ በአግባቡ ማስረዳት ይጠበቃል:: በቀጣይም የምንሄድበት ጉዳይ ነው:: በሊዝ አዋጁ ስጋት የሚፈጥር ምንም ነገር እንደሌለ ነው እኔ የምገነዘበው:: በተለይ ሽያጭን በተመለከተ:: ካነሳችሁት ጥያቄ አንፃር ለምሳሌ አንድ ሰው ይዞታውን ይሸጣል:: የተሸጠውን ይዞታ ሲያስተላልፍ ወደ ሊዝ ሥሪት ይገባል:: ይህ እንግዲህ በቤተሰብ መካከል የተለያየ አምባጓሮ እየፈጠረ ነው:: ይህ የሚፈጸመው ነባር ሥሪት ላይ ያለ ንብረት ለመሸጥ የሚከላከል ነገር የለም:: ይሸጣል:: ሲሸጥ ግን እንደምታውቁት መሬት በዚህች አገር የሕዝብና የመንግሥት ሀብት ነው:: ንብረቱ በሚሸጥበት ጊዜ በተገኘው ዋጋ ይሸጣል:: ይኼ የመሬት ዋጋ ነው? ይኼ የቤቱ ዋጋ ነው? አይለይም:: እንዲሁ ይሸጣል:: ነገር ግን ለስም ዝውውር በሚመጣበት ጊዜ የስም ዝውውሩ የሚደረገው በሊዝ አግባብ ነው የሚሆነው:: በሊዝ አግባብ ሲዛወር አንዱ መነሻ ዋጋውን መሠረት አድርጎ ነው:: ይህ መነሻ ዋጋ እንግዲህ አዲስ አበባ በየትኛውም ቦታ ብትሄዱ መነሻ ዋጋው ከ600 ብር አይበልጥም::

ለምሳሌ አንድ ሰው በ200 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያለ ንብረቱን ሲሸጥ ይህ ቦታ የሚገኝበት አካባቢ ያለው መነሻ ዋጋ በካሬ ሜትር 500 ብር ቢሆን 200 ሲባዛ በ500 ይሆናል 100 ሺሕ ብር ነው:: የሊዝ ዋጋው 100 ሺሕ ብር ነው ማለት ነው:: በሊዝ ውል ላይ በተቀመጠው መሠረት ከዚህ ገንዘብ ላይ 10 በመቶ ነው የሚከፍለው ወደ ስም ዝውውር ሲገባ:: ይህንን ይከፍልና ቀሪውን ዘጠና በመቶ በሊዝ ውል በተቀመጠው መሠረት በ30

ወይም በ40 ዓመት አጠናቆ ይጨርሳል ማለት ነው:: ይህ ማለት አንደኛ ይህ መሬት ለገዢው አካል ዋጋ (ቫሊዩ) እንዲኖረው ያደርገዋል:: የሊዝ ዋጋ ይኖረዋል፤ የሊዝ ዋጋ የሚሰጣቸው መብቶችና ጥቅሞች አሉ:: ከነባር ይዞታ ይልቅ:: አሁን ይህ ዋጋ በዋስትና ለማስያዝና በከፈለው መጠን እዚያው ላይ ባለው መጠን በዋስትና ለማስያዝና ተጠቃሚ ለመሆን ያስችላል:: ሁለተኛ አንዴ ውል ሲገባ 30 ዓመትም ይሁን 40 ዓመት ውል በገባበት ወቅት ከሚከፍለው የሊዝ ክፍያ ጋር ተመሳሳይ ነው:: በነበረው ነባር የይዞታ ሥርዓት ቢሆን ሰውየው የሚከፍለው በየወቅቱ በሚከለሰው ግብር ነው:: በየዓመቱ ሊጨምር ይችላል::

በየወቅቱ የማይጨመር ክፍያ ነው በየጊዜው ለሊዝ ኪራይ የሚከፍለው:: ሁለተኛ ለሕዝብ ጥቅም ተብሎ ከቦታው ላይ ሲነሳ ተመሳሳይ ስፋትና ደረጃ ባለው ቦታ ላይ ነው ልዋጭ የሚሰጠው:: ስለዚህ ጥቅሙ ያለው ወደ ሊዝ የተሸጋገረለት ሰው ነው:: ይህ ሲታይ መንግሥት ቀደም ሲል መረጃዎች ላይ ካያችሁ የመሬት ዋጋ ይህን ያህል የሚል አለው:: የንብረቱ ይህንን ያህል የሚል አለው ከዚያ ያቺ የተተመነችውን ነው የሚከፍለው:: ይህ ተተምኖ ነው ክፍያ የሚፈጸመው:: ቀድሞ ሲከፈል የነበረው አሹራ በአዲሱ አዋጅ ወደ ሊዝ ሲዞር በሊዝ ክፍያ ይተካል:: ይህ ማለት በጣም ኢምንት የሆነ ክፍያ ነው የሚከፍለው:: ስለዚህ በግለሰቦች ላይ የሚያመጣው ተፅዕኖ የለም::

በውርስ የተገኘ ይዞታ

የግል ባለይዞታ ሆነው በውርስ ከአንድ ሺሕ እስከ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ካሬ ሜትር ወይም ሰፋ ያለ ይዞታ በውርስ ያገኙ ሰዎች አሉ:: እነዚህ በውርስ ያገኙ ሰዎች ቦታውን በውርስ ያገኙ በመሆኑ አዋጁም ከውርስ በስተቀር ስለሚል አይከፍሉም:: በሌሎች ክፍለ ከተሞች ደግሞ ይከፍላሉ አሠራሩ ወጥ አይደለም የሚባል ነገር አለ:: ለነገሩ አሁን ባለው ሁኔታ አዋጁ ተግባራዊ አልተደረገም:: የሽግግር ጊዜ ተቀምጦለታል:: ስለዚህ አሁን ባለው ሁኔታ ክፍለ ከተሞች አንተ ትከፍላለህ አንተ አትከፍልም የሚያስብል ነገር የለም:: አዋጁ ሦስት ወር የሽግግር ጊዜ አስቀምጧል:: በዚህ አግባብ ላይ ያለ ውርስ የቀረበበት ምክንያት ምንድን ነው? ለውርስ የማይከፈልበት ምክንያት ምንድን ነው? የሚሉ ነገሮን ማየት ተገቢ ነው:: አንዱ ውርስ ሲሆን ‹‹ኖርማል ትራንዛክሽን›› አይደለም የሚፈጸመው:: የፍትሐ ብሔር ሕጉ ውርሱ ለሚገባቸው አካላት ነው ይዞታው የሚተላለፈው ይላል:: ይህ መብት ያላቸው አካላት ደግሞ ትራንዛክሽን ውስጥ ለመግባት ያላቸው የኢኮኖሚ ሁኔታ ዝግጁ ካለመሆኑ አንፃር ትራንዛክሽን ሊፈጸም አይችልም:: በመሆኑም መብታቸው መተላለፍ ካለበት ተነጣጥሎ መቅረት የለበትም ስለዚህ እንዲተላለፍላቸው ይደረጋል:: ግን በቀጣይ እነዚህም ቢሆኑ በሚጠናው ጥናት መሠረት ከኅብረተሰቡ ጋር ውይይት ተደርጎ በቀጣይ ከነባር ይዞታ ሥሪት ወደ ሊዝ ሥሪት በሚሸጋገርበት ጊዜ የሚፈጸም ነው የሚሆነው:: በጥናቱ ይህንን ያህል ካሬ ቦታ ያለው ሰው ምን ያህል ይከፍላል የሚል ቀጣይ አጠቃላይ ጥናት ተደርጎ መልስ

የሚሰጥበት ይሆናል::

የባዶ መሬት ሽያጭ

አንድ መንግሥት በሊዝ አግባብ ቦታ ሲሰጥ ቦታው ቀጥታ ለልማት ውሎ፣ የሥራ ዕድል ፈጥሮ፣ ኢኮኖሚውን አሳድጎ፣ ሌሎች ተጨማሪ ጥቅሞችን እንዲያመጣ ነው:: ባዶ መሬት እንዲገላበጥ አይደለም የመንግሥት ፍላጎት:: ይሁንና ግን እነዚህ መጠነኛ ግንባታ የገነቡ ሰዎች ግንባታውን ለመቀጠል አቅም ሊያጥራቸው ይችላል:: በተወሰነ ደረጃ ላይ የተወሰነ የአቅም ማነስ ተፈጥሮ ሊሆን ይችላል:: ይህ በሚሆን ጊዜ አዋጁ በግልጽ አስቀምጧል:: ሰውየው መብቱን ማስተላለፍ ይችላል:: አይደለም ግንባታ ከግማሽ በታች አከናውኖ ይቅርና የግንባታ ዘመኑ እስካላለፈ ድረስ ባዶ መሬትም ማስተላለፍ ይቻላል:: ነገር ግን ይህንን ይዞታ ሲያስተላልፍ ይህ ሰው በዚያ ቦታ ላይ ያለው ዋጋ፣ የመሠረተ ልማት፣ የግብይት ዋጋ ከፍ ማለት፣ ጥቅሞች የተገኙት በመንግሥት በተካሄዱ ሥራዎች እንጂ ሰውየው የሠራቸው አይደሉም:: ለውጡ የመጣው ከተሞች መሠረተ ልማት ዘርግተው ሀብታቸውን አፍሰው ባመጡት ጥቅም ነው::

ሻጩ ቦታውን ሲያስተላልፍ የንብረቱን ዋጋ ማለትም ለሊዝ የከፈለውን ቅድመ ክፍያ ማግኘት ይችላል:: ይህ ገንዘብ በባንክ ቢቀመጥ ወለድም ያገኛል:: ከተገኘው የመሬት ዋጋ ልዩነቱን አምስት በመቶ ያህሉን ይሰጠዋል:: ለለፋበት ወዲህ ወዲያ ላለበት ማለት ነው:: በዚህ አግባብ ክፍያው ይፈጸማል:: የሚተላለፍለት ግለሰብ ግን የሊዝ ውሉን ቀደም ሲል በ18 ወር ይጠናቀቃል ተብሎ ውል ከተፈጸመ አዲሱ ውል ተቀባይም በዚህ ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እርግጠኛ መሆን ይኖርበታል:: ነባር ይዞታን ወደ ሊዝ ሥሪት ሲገባ ይኼ አዋጅ ላይ በግልጽ ተቀምጧል:: ነባር ይዞታ ወደ ሊዝ በሚሸጋገርበት ጊዜ ጥናት ተደርጎ ነው:: አራት ዓመት የተሰጠው ለጥናት ነው:: በዚህ ጊዜ ውስጥ ጥናት ተደርጎ ከኅብረተሰቡ ጋር በቂ ውይይት ተደርጎበት ወደ ሊዝ ሥርዓት የሚሸጋገርበት አግባብ ይኖራል:: ወደ ሊዝ ሲሸጋገር በመነሻ ዋጋ ነው የሚተላለፈው:: ነገር ግን ይህንን ጥናት ሳይጠብቅ የሚሸጋገሩ ነገሮች ተለይተው ተቀምጠዋል:: አንዱ በትራንዛክሽን ጊዜ ይህ ጥናት ሳይጠበቅ ወደ ሊዝ እንዲገባ ይደረጋል::

ሁለተኛው በሕገወጥ አግባባ የየተያዘ መሬት ሕጋዊ እንዲሆን ከተሞች ሲወስኑ ቀድሞ በዚያ መሬት የተከፈለ ነገር የለም፤ አግባብ በሆነ አካል የተሰጠ ቦታም አይደለም:: ከተሞች ይህንን ቦታ ወደ ሊዝ ሥርዓት እንዲገባ ሲያደርጉ በሊዝ አግባብ ይሆናል:: ሌላው ሁለት ይዞታዎች ሲቀላቀሉ ሊዝ ይሆናል:: ማለትም አንድ ሰው ነባር ይዞታ አለው:: እዚያ አጠገብ ቦታ በሊዝ ቢገዛና መቀላቀል ካሰበ ቦታው በሊዝ ሥሪት ይገባል:: እንዲሁ እንዲቀጥል ከፈለገ ይዞታው ወደ ሊዝ ሳይገባ ይቀጥልበታል:: ይቀላቀል ሲል ነው ወደ ሊዝ ሥሪት የሚገባው:: ሰውየው ለነባር ይዞታው የሚከፍለው በአካባቢው የቦታ መነሻ ዋጋ ይሆናል:: ካርታው አንድ ላይ ይዘጋጅለታል:: ከዚያ ወደ ውል ይኬዳል:: በሚወጣው ደንብ ላይ በደንብ የሚዘረዘሩ

ነገሮች ይኖራሉ::

የሊዝ ዘመን ዕድሳት

አዋጁ ሊዝ ሊታደስ በማይችልበት ሁኔታ ካሳ አይከፈልም ይላል:: ሊዝ የማይታደስበት ሁኔታ አለ ወይ? እንግዲህ ለአንድ የሊዝ ዘመን ለመኖርያ ቤት ለምሳሌ በሊዝ ቦታ ተወስዷል:: ካርታው ቢታይ ለ99 ዓመት የሊዝ ዘመን ይላል:: ለንግድም ሆነ ለሁሉም የሊዝ ዘመን ተቀምጧል:: ይህን ወስዶ ልማቱን እየፈጸመ ሲኖር ቆይቶ 89 ዓመት ይደርሳል:: አዋጁ እንደሚለው ከ10 ዓመት በፊት ለሊዝ ዕድሳት ማመልከት ስላለበት እዚህ ዘመን ላይ ሲደርስ ይታደሳልኝ ብሎ ይቀርባል:: በሚቀርብበት ጊዜ እንግዲህ በ100 ዓመት ዕድሜ የአንድ ከተማን ዕድገት ማሰብ ትችላላችሁ:: በአዲስ አበባ አይደለም በመቶ ዓመት ባለፉት 10 እና 20 ዓመታት የመጣውን ለውጥ ታስተውላላችሁ::

ከዚህ ለውጥ ተነስቶ ያ ቦታ በሚጠናው ማስተር ፕላን መሠረት አሥር ዓመት ለማስተር ፕላን የተሰጠው ዕድሜ ነው:: በማስተር ፕላኑ መሠረት ቦታው ለሌላ ልማት እንዲውል ነው የተወሰነው እንበል:: በማስተር ፕላኑ ከዚያ በኋላ ይኼ ቦታ አይታደስም:: በቀጣይ ሌላ ልማት ነው የሚካሄድበት ተብሎ ተወስኗል:: ስለዚህ ካሳ አያገኝም ማለት ነው:: ካሳ የማያገኘው በሊዝ የተሰጠ መሬት መቶ ዓመት ካገለገለ በኋላ ካሳ አይገባውም:: አይደለም አንድ መሬት አንድ አገር ለምሳሌ ታይላንድን ውሰዱ እንግሊዞች በሊዝ ወስደው ገነቡ:: ከ90-100 ዓመት ኖሩ:: የሊዝ ዘመኑ ሲጠናቀቅ ወጡ ማለት ነው:: አንድ የተከፈለ ካሳ የለም:: በተሰጣቸው የሊዝ ዘመን ተጠቅመዋል:: ግለሰቡ የሚገባውን ተጠቅሟል ተብሎ ነው የሚታመነው:: ስለዚህ ካሳ አይገባውም:: ንብረቱን ማንሳት ብቻ ነው::

በምደባ ቦታ ስለመስጠት

ተተኪ ቤት ማግኘት የማይቻል ሲሆን ለምሳሌ መልሶ ማልማት ቦታ ላይ ተከራዮች አሉ:: ከቀበሌ ከመንግሥት የተከራየ አለ:: የመጀመርያው የሚሆነው ኮንዶሚኒየም በሚገነባባቸው ከተሞች ኮንዶሚኒየም እንዲያገኙ ማስቻል ነው:: በአዲስ አበባ እየተፈጸመ ነው:: ኮንዶሚኒየም በማይገነባባቸው ከተሞች ግን እነዚህ ተነሺዎች እንዲደራጁ ተደርጎ በሚያስቀምጡት የገንዘብ መጠን፣ እዚህ ላይ ሰውየው ቁርጠኛ ሆኖ ገንዘብ ማጠራቀም አለበት:: ሲያጠራቅም 60 በመቶውን መንግሥት ያበድረዋል:: ቦታውን ያለማል:: 40 በመቶ ገንዘብ አስቀምጦ ማልማት ካልቻለ ወይም ካልፈለገ ሦስት በመቶ ተቀጥቶ ገንዘቡን [ያስቀመጠውን] ይወሰዳል:: ምንም የሌለው ከሆነስ? ምንም የሌለው ከሆነ በተለያዩ የመልሶ ማልማት ቦታዎች ላይ እንደሚደረገው ተለዋጭ የቀበሌ ቤት ይሰጠዋል::

ነባር ይዞታ ወደ ሊዝ ሲገባ ሕገ መንግሥቱ ያስቀመጠውን ንብረት የማፍራት ዋስትና አይጥስም?

በሊዝ በወሰደው መሬት ላይ ንብረት ማፍራትና በነባር ይዞታ ላይ ንብረት ማፍራት የትኛው ነው ለአልሚው ጥቅም ያለው? ይህ አዋጅ ሕገ መንግሥቱ ያስቀመጠውን ነው ይዞ የሄደው:: ሊዝ ሲሆን ይህ መብት ይሸረፋል ወይ ነው? ሊዝ ሲሆን እንዲያውም የተሻለ ተጠቃሚ ያደርገዋል እንጂ ጉዳት የለውም:: በሊዝ ሥርዓት ያውም ገና ጥናቱ ተጠናቆ ከአራት ዓመት በኋላ የሚወሰን ውሳኔ ነው:: እሱም ሆኖ ሳያበቃ አሠራሩ ንብረት የማፍራትን መብትን ያጠናክረዋል እንጂ የሚሸረሽርበት አግባብ የለውም:: አንድ ሰው ንብረት ሲያፈራ በዋስትና እንዲያዝለት የማድረግም ጭምር ነው:: ንብረት ማፍራት ብቻውን ምንም አይደለም:: ንብረት ማፍራት ዋስትና ሲኖረው ነው ጥቅም ያለው:: ይኼ አዋጅ ምንድን ነው ያደረገው? ይህ ንብረት ወደሊዝ ሲመጣ የሊዝ ዋስትናን ነው የሚያጎናጽፈው:: ስለዚህ ዋስትናው በተጠናከረ ሁኔታ ከመሬቱና ከንብረቱ ጋር ባለበት ሁኔታ ይቀጥልለታል:: የመያዣ ዋስትናው ይጠናከርለታል:: ከዚሁ ጋር በተለይ ከማይንቀሳቀስ ንብረት ምዝገባ ጋር የሚመጡ አሠራሮች ይኖራሉ:: ይህን ሁኔታ የበለጠ ያጠናክርለታል:: መብቱን ሰፋ ያደርግለታል:: ወደ ሊዝ ሲገባ መብቱ ከመሸርሸር ይልቅ እንዲያውም ይጠናከራል:: በነባሩም ይዞታ ይህ መብት የተሸራረፈበት ሁኔታ የለም:: ተጠናክሮ ነው ያለው:: በሊዝ ሥሪት ደግሞ ሀብት የማፍራት ጉዳይ የበለጠ ዋስትና ይኖረዋል::

ከገጽ 36 የዞረ

ጽሕፈት ቤቶቹ መዘጋታቸውን ይናገራሉ:: እርሳቸው እንደሚሉት፣ ፓርቲው በገጠመው የገንዘብ እጥረት ምክንያት በአገሪቱ ከከፈታቸው 62 ጽሕፈት ቤቶች መካከል አሁን የቀሩት ቃሊቲና ሳውላ ያሉት ሁለት ጽሕፈት ቤቶች ብቻ ናቸው::

‹‹በአሁኑ ጊዜ በክልልና በአዲስ አበባ ያሉ ጽሕፈት ቤቶች በመዘጋታቸው አባላቱ እየተበተኑ ነው፤ የጽሕፈት ቤቶቹ ንብረት በዕዳ እየተያዘ እየተሸጠ ነው፤›› የሚሉት መቶ አለቃ ፍቃዱ፣ ፓርቲው ውስጥ በተፈጠረው የውስጥ ችግር ምክንያት አባላቱ እንደ ፓርቲ ተሰብስበው በአሁኑ ጊዜ በሌሎች ድርጅቶች ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር እንኳን ማውገዝ አለመቻላቸውን ይገልጻሉ::

የፓርቲው ዋና ጸሐፊ አቶ ታሪኩ በበኩላቸው፣ መኢአድ ከከፈታቸው 62 ጽሕፈት ቤቶች መካከል ስልሳዎቹ ተዘግተዋል የሚለው መረጃ የተጋነነ መሆኑን ቢገልጹም፣ በፓርቲው ውስጥ በተፈጠረው ችግር ምክንያት አብዛኛዎቹ ጽሕፈት ቤቶች መዘጋታቸውን አምነዋል::

መኢአድ የኢንጂነር ኃይሉ ሻውል የግል ድርጅት ሆኗል በሚል በመቶ አለቃ ፍቃዱ ለቀረበው ትችት ሲመልሱም፣ ‹‹ጋሽ ኃይሉ የተጣለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት በተቻለ መልኩ የዚህ ቤት ምሰሶ ሆነው እየሠሩ ነው፤ ፓርቲውንም ማቆየት የተቻለው በእሳቸው ነው፤›› በማለት ውንጀላው መሠረተ ቢስ መሆኑን ይናገራሉ::

መኢአድ...

ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ደሳለኝ አምባውና የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እስራኤል ተስፋዬ

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/ናሆ

ም ተ

ስፋዬ

Page 6: Reporter Issue 1201

ገጽ 6|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

ዲሪባ ደፈርሻ የመንገድ እና የውሃ ሥራዎች ተቋራጭ

( 251-11-651-41-52፣ 011-618-26-82 ፋክስ 011-618-26-85

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያድርጅቱ ቀጥሎ ክፍት የሥራ መደቦች ላይ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

ተ.ቁየሥራ መደቡ

መጠሪያየትምህርት

ደረጃየሥራ ልምድ ብዛት

1 ኢኩዩፕመንት ማኔጀር

በመካኒካል ኢንጅነሪንግ በዲፕሎማ የተመረቀ

በሙያው 6 ዓመት የሠራ

2

ደመወዝ፡ በስምምነት

የሥራ ቦታ፡ በልታ ኦቶሎ (አርባ ምንጭ)

ከላይ የተጠቀሱትን መመዘኛዎች የምትሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃ ኦሪጅናሉንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ መገናኛ አካባቢ ለም ሆቴል ፊት ለፊት ወደ ቀበሌ 24 የሚያመራው አዲስ የተሠራው መንገድ በስተግራ አቅጣጫ በሶስቱ ጓደኛሞች የወንዶች ሳሎን በኩል ወደ ግራ በሚታጠፈው አስፋልት ወደ ትልቅ ግቢ ገባ ብሎ በሚገኘው የድርጅቱ ጽ/ቤት በግምባር በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-651-41-52/011-618-26-82 ደውሎ መረዳት ይቻላል፡፡

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያተ.ቁ የሥራ

መደብየትምህርት ደረጃ የሥራ ልምድ

1 ኦፊስ ኢንጅነር

በሲቪል ምህንድስና የቢ.ኤስ.ሲ ዲግሪ ያለው/ላትወይምየኮሌጅ ዲፕሎማ ያለው

በወርድ፣በኤክስኤል እና ኤምኤስ ፕሮጀክት በቂ ችሎታ ያለው/ላት ሆኖ በሕንፃ ሥራ ፕሮጀክት ቢያንስ 3/ሶስት/ ዓመትና ከዚያ በላይ የሠራ/ችወይምበሕንፃ ሥራ ፕሮጀክት ላይ ቢያንስ 5/አምስት/ ዓመትና ከዚያ በላይ የሠራ/ች

2 ሳይት ኢንጅነር

በሲቪል ምህንድስና የቢ.ኤስ.ሲ ዲግሪ ያለው/ላትወይምየኮሌጅ ዲፕሎማ ያለው

በህንፃ ሥራ ፕሮጀክት ላይ ቢያንስ 3/ሶስት/ ዓመትና ከዚያ በላይ የሠራ/ች ወይምበሕንፃ ሥራ ፕሮጀክት ላይ ቢያንስ 5/አምስት/ ዓመትና ከዚያ በላይ የሠራ/ች

3 ሰርቬየር በሰርቬይንግ የኮሌጅ ዲፕሎማ ያለው

በቶታል ስቴሽን አጠቃቀም በቂ ልምድ ያለው/ላት ሆኖ በተመሳሳይ የስራ መስክ 2/ሁለት/ዓመትና ከዚያ በላይ የሠራ/ች

ደመወዝ፣ በስምምነት

የሥራ ቦታ፣ አዲስ አበባ /አይ.ሲ.ቲ.ፓርክ ሕንፃ ፕሮጀክት/

ከዚህ በላይ በተመለከቱት የሥራ መደቦች ለመወዳደር የምትፈልጉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ5/አምስት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የትምህርት ማስረጃ እና የሥራ ልምዳችሁን በመያዝ አስተዳደር ክፍል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

አድራሻ፣ ብስራተ ገብርኤል ቤክርስርስያን ጀርባ የድሮ አይሮፕላን ማረፊያ አካባቢ ሳትኮን ዋናው መ/ቤት ስልክ ቁጥር 011 372 78 22 ወይም 011 372-71-74

‹‹ኤርትራ እንደ አንድ አገር የመቀጠል ዕድሏ እየጨለመ ነው››

ሪፖርተር፡- የቀይ ባህር አፋርን የወደፊት ዕጣ ፈንታ አስመልክተው ባካሄዱት ጥናት አንዳንድ ድምዳሜዎች ላይ ደርሰዋል:: ኤርትራ ውስጥ ስላለው የአፋር ሕዝብ የወደፊት ዕድል ምን ያስባሉ?

ፕ/ር ዮሴፍ፡- የውይይቱ ዋነኛ ማዕከል ነጥብ የኤርትራን የቀይ ባህር አፋር ሕዝብ የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚመለከት ነው:: እንደኔ እምነት ኤርትራ የምትባል አገር ከዚህ በኋላ እንደ አንድ አገር የመቀጠል ዕድሏ እየጨለመ ነው:: ብዙ ጊዜ ትቆያለች የሚል እምነት የለኝም:: የኤርትራ አንድነት ምንም ሆነ ምን፣ ጥያቄው የአፋር ሕዝብ ዕድልስ ምን ይሆናል? የሚል ነው:: ዛሬ ጠዋት እዚሁ ቤት ውስጥ ውይይት የተረገበትም ይኼው ጉዳይ ነበር::

የእኔ ሐሳብ የኤርትራ ሕዝብ በአንድነት መቀጠል የሚችለው የአፋርን ሕዝብ ጨምሮ የእያንዳንዱን ብሔረሰብ ማንነት ያከበረ የፌዴራል ሥርዓት ከተቋቋመ ብቻ ነው የሚል ነው:: የእያንዳንዱን ብሔረሰብ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ያከበረ ሥርዓት ማቋቋም ግድ ይላል:: ይኼ ደግሞ ኢትዮጵያን ጨምሮ የተለያዩ ብሔረሰቦችና ቋንቋ ያላቸው አገሮች የሚከተሉት የፌዴራል ሥርዓት ነው:: በተለይ ደግሞ በብሔረሰብ ማንነት ላይ የተመሠረተ ፌዴራሊዝም ለኤርትራም የሚመከር ነው:: ኤርትራ ውስጥ ላለው አጠቃላይ ቀውስ መፍትሔው ይኼን ሥርዓት መተግበር ብቻ ነው::

ይኼ በ1983 ዓ.ም. አዲሱ የኤርትራ መንግሥት እንዲከተለው የተመከረው ሥርዓት ነበር:: የኤርትራ አፋርን ጨምሮ ኤርትራ ውስጥ ያሉት ብሔረሰቦች የተዋጉለት ነፃነት ይኼው ነበር:: ራሳቸውን በራሳቸው የማስተዳደር መብት እንዲኖራቸው ይፈልጋሉ:: የሁሉንም ብሔረሰቦች መብት እኩል የሚመለከትና የሁሉንም መብት የሚያስከብር ሥርዓት

ፕሮፌሰር ዮሴፍ ማግኔታ

ፕሮፌሰር ዮሴፍ ማግኔታ

ቀይ ባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት የኤርትራ ቀይ ባህር አፋር ሕዝብን ‹‹ራስን በራስ የማስተዳደር እስከመገንጠል›› መብት ለማረጋገጥ በትጥቅ ትግል ላይ የተሰማራ ድርጅት ነው:: ድርጅቱ ጥቅምት 13 ቀን 2004 ዓ.ም. የተጠናቀቀውን 3ኛ ሕዝባዊ ኮንፈረንስ በሰመራ (አፋር) አካሂዷል::

በኮንፈረንሱ ከ3,500 በላይ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን፣ በኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና በሌሎች የአገሪቱ ባለሥልጣናት ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል ክስ እንዲመሠረት ለተባበሩት መንግሥታት

ድርጅት (ተመድ) ጥያቄ ቀርቧል:: ሰነዱን አጠናቅረው ያቀረቡትና ጉዳዩን በኃላፊነት እየተከታተሉት ያሉት ካናዳዊው የሕግ ፕሮፌሰር ዮሴፍ ማግኔታና ካንጎ አፋር ድርጅት ናቸው:: በኮንፈረንሱ ላይ የተገኘው የማነ ናግሽ ጉዳዩን በማስመልከት ከፕሮፌሰር ዮሴፍ ማግኔታና ከካንጎ አፋር ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዋረን ክሬአትስ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል::

ነው:: ሪፖርተር፡- ኢትዮጵያ ውስጥ ተመሳሳይ ሥርዓት እየተሞከረ

ነው:: ነገር ግን እሱም ቢሆን ሙሉ ለሙሉ መፍትሔ አላስገኘም ተብሎ እየተተቸ ነው:: ኤርትራ ይኼን ሥርዓት እንድትከተል እንዴት ይመክራሉ?

ፕ/ር ዮሴፍ፡- እስቲ የኢትዮጵያን ታሪክ እንመልከት:: በብሔር ላይ የተመሠረተ ፌዴራላዊ ሥርዓት ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት የነበረው ሁኔታ የብሔር ጭቆናን፣ ግጭትን፣ ጦርነትን፣ ኋላቀርነትን፣ የአንድን ብሔር የበላይነትን፣ ወዘተ እናገኛለን:: ይኼው ሥርዓት ተግባራዊ ከሆነ ካለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት በኋላ ያለውን ሁኔታ ስንመለከት ግን የተሻለ ሰላምና መረጋጋት፣ ልማትና ብልፅግናን እናገኛለን:: የኤርትራ መንግሥትም ተመሳሳይ ሥርዓት ተግባራዊ አድርጎ ቢሆን ኑሮ የተሻለ ሰላምና መረጋጋት ይኖር ነበር:: አሁን ግን የምናየው ከአንዱ ቀውስ ወደ ሌላ ቀውስ ስትገባ ነው::

ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ካሉት አገሮች መካከል ነች:: እያንዳንዱ ሰው የመሰለውን የመናገር መብት አለው:: ይኼን ሥርዓት የሚቃወምም በአገር ውስጥ በሰላም እየኖረ ነው:: ሁልጊዜ ደግሞ ተቃውሞ አይኖርም አይባልም:: ግን ምን ያህል ሰው ነው ይኼንን ሥርዓት የሚቃወመው? ነው ጥያቄው:: ኢትዮጵያ ውስጥ እየሆነ ያለው በአብዛኛው ዓለም እየሆነ ያለው ነው:: እነ ካናዳ፣ ቤልጂየም፣ ስዊዘርላንድ የመሳሰሉ የበለፀጉ አገሮች ይኼንን ሥርዓት ተከትለው ነው የተሻለ ሰላምና መረጋጋት የፈጠሩት::

ኤርትራም ውስጥ ያለው አጠቃላይ ቀውስ መፍትሔው ይኼው ብቻ ነው:: በእርግጥ የሕዝቡን ምርጫ ማስቀደም ትልቁ ነገር ነው::

ሪፖርተር፡- እዚህ ኢትዮጵያ (አፋር ክልል) ውስጥ በርካታ የቀይ ባህር አፋር ሕዝብ ተወላጆች በስደት እየኖሩ ነው:: የማነጋገር ዕድል አግኝተው እንደሆነ የስደተኞቹ ፍላጎት ምን ይመስላል? ኮንፈረንሱንስ እንዴት አገኙት?

ፕ/ር ዮሴፍ፡- እዚህ ኮንፈረንስ ላይ የተላለፉ ውሳኔዎች አሉ:: በኮንፈረንሱ ውስጥም የቀይ አፋር ድርጅት አመራሮችና በስደት የሚገኘው የቀይ ባህር አፋር ሕዝብ ተገኝቷል:: ስለዚህ የሕዝቡ የፖለቲካ አመራሮች፣ ሴቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የጎሳ መሪዎች እንዲሁም ደግሞ በአካባቢው በሰብዓዊ ዕርዳታ ላይ የሚሠሩ ድርጅቶች ተሳትፈውበታል:: እነዚህ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የአፋርን ሕዝብ ፍላጎት የሚወክሉ ናቸው::

Page 7: Reporter Issue 1201

|ገጽ 7 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

ስለዚህ እዚህ ኮንፈረንስ ውስጥ የተወሰዱ ውሳኔዎችና የቀረቡ ሐሳቦችም ሕዝቡ ምን ሁኔታ ላይ እንዳለና ምን እንደሚፈልግ አመላካች ናቸው:: እንዲሁም ደግሞ ኤርትራ ውስጥ ምን መደረግ እንዳለበት የሚያመላክቱ ሐሳቦች ቀርበዋል::

ሪፖርተር፡- የኤርትራውን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን በዘር ማጥፋት የሚያስወነጅል ክስ ለተመድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰነድ አቅርበዋል:: ሕዝቡም እንዲፈርም ‹‹ፔቲሽን›› እየተሰበሰበ ነው:: ስለእሱ ቢነግሩኝ?

ፕ/ር ዮሴፍ፡- የኤርትራ መንግሥት በቀይ ባህር አፋር ላይ የሚፈጽመው ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት አሳስቦናል:: ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ ከካንጎ አፋር ድርጅት ጋር በመተባበር በአፋር ሕዝብ ላይ የተፈጸመውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ ወንጀል በሰነድ አስደግፈን አዘጋጅተናል:: ሰነዱን ያቀረብነውም ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ነው:: አቀራረባችን በሁለት ጉዳዮች ላይ በማተኮር ሲሆን፣ በበቂ ማስረጃ የተደገፈ ነው:: የተፈጸመውን ጭቆና ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይና በብዙ አሥር ሺሕ የሚቆጠር የአፋር ሕዘብ አገሩን ለቆ እንዲሰደድ ያስገደደ መሆኑን የሚያሳይ ነው:: እነዚህ ሰዎች እዚህና በተለያዩ ቦታዎች በስደት እየኖሩ የሚገኙ ናቸው::

በመሆኑም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቀረብነውን ሰነድ ተመልክቶ እዚህ ድረስ ሰዎች ልኮ እንዲያጣራና ጉዳዩን እንዲመረምር ጠይቀናል:: እንዲሁም ደግሞ ተመድ ጉዳዩን አጣርቶ በዚህ ጉዳይ ተጠያቂ በሆኑት የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና በሌሎች ተባባሪዎቻቸው ላይ በዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ እንዲመሠረት ጠይቀናል::

ሪፖርተር፡- የተመድ ምላሽ ምን ይመስላል?ፕ/ር ዮሴፍ፡- በተለይ ከድርጅቱ ልዩ አገር በቀል

መብቶች ቢሮ (Office of Special Indigenous Rights) ጋር ተነጋግረናል:: ቢሮው ያቀረብነውን ሰነድ ተመልክቶታል:: እኛም በዚህ መሠረት ተመድ የራሱን ልዩ ልዑክ ወደ ቦታው አሰማርቶ እንዲመረምር ጠይቀናል:: በተጨማሪም ከተመድ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ዳኞች ጋር እየተነጋገርን ነው:: እነሱም ያቀረብነውን ሰነድ እንደተመለከቱት አውቀናል፤ ገልጸውልናልም:: የኤርትራ መንግሥት በቀረበው የክስ መነሻ ሰነድ ላይ አስተያየቱን እንዲሰጥ ቢጠየቅም፣ የኤርትራ ባለሥልጣናት ፈቃደኞች አይደሉም::

ሪፖርተር፡- የካንጎ አፋርን እንቅስቃሴን እንዴት ይገልጹታል?ዶ/ር ዋረን ክሬኤትስ፡- ከአምስት ዓመት በፊት ነው

ይህንን ቦታ ለመጀመርያ ጊዜ የረገጥኩት:: የአፋር ሕዝብ ፍላጎት ምንድን እንደሆነ ተገንዝቤ ሄድኩና ከሚስተር ዮሴፍ መሐመድ ጋር በመተባበር ካንጎ አፋር ድርጅትን ለማቋቋም ቻልን:: ከአቅም ግንባታ፣ ከዕርዳታና ከሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ጋር በተያያዘ እየሠራን እንገኛለን:: ከአቅም ግንባታ ጋር በተያያዘ፣ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሠርተን እየሠራን ነው:: ለአካባቢው ሕዝብ ንፁህ ውኃ ለማቅረብም እየሠራን ነው::

በተለይ ደግሞ ኤርትራ ውስጥ ባለው የፖለቲካ ችግር ምክንያት በርካታ ሕዝብ ወደዚህ ክልል በስደት እየመጣ

ስለሆነ፣ ባለፉት አምስት ዓመታት ሰብዓዊ ዕርዳታ ስናደርግ ቆይተናል:: በተለይ ደግሞ ነፍሰ ጡሮችና ሕፃናት በምግብ እጦት ምክንያት ሕይወታቸውን እንዳያጡ እያደረግን ነው::

በተጨማሪም በዚህ አምስት ዓመት ከቀይ ባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን፣ የኤርትራ መንግሥት በአፋር ሕዝብ ላይ ለፈጸመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠያቂ ለማድረግና ወደ ሕግ ለማቅረብም እንሠራለን:: ሕዝቡን በእንዲህ ዓይነት ጉዳዮች በማሳተፍ ድምፁን ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ እንዲያሰማ እያደረግን ነው::

ሪፖርተር፡- በእነዚህ አምስት ዓመታት ውስጥ ምን ዓይነት ለውጦችን ተመልክታችኋል?

ዶ/ር ዋረን ክሬኤትስ፡- ከኤርትራ የሚመጣው የስደተኛ ቁጥር እጅግ እየጨመረ ነው ያለው:: በዚህ ድንበር በኩል

በየቀኑ የሚገባው ስደተኛ ቁጥር በየትኛውም የዓለማችን አካባቢ ያለ አይመስለኝም:: ይኼ ደግሞ በዚሁ የአፋር ማኅበረሰብ (ኢትዮጵያ) ላይ፣ በኢትዮጵያ መንግሥትና በአፋር ክልላዊ መንግሥት ላይ ጫና እየፈጠረ ነው:: በየቀኑ በጣም እየጨመረ ላለው የስደተኞች ቁጥር አስፈላጊውን የሰብዓዊ ዕርዳታ ማቅረብ ከባድ እየሆነ መጥቷል:: ከአምስት ዓመታት በፊት ወደዚህ አካባቢ ስመጣ የስደተኞች ካምፕ አልነበረም:: የተባበሩት መንግሥታት ካምፕ ለማቋቋም እያሰበ ነበር:: አሁን እዚህ ብቻ የተመዘገቡ ከ30 ሺሕ በላይ ስደተኞች አሉ:: እናም የሚቀርበው የሰብዓዊ ዕርዳታ አገልግሎት በቂ አይደለም::

በአጭር ጊዜ ለውጥ ለማየት እመኛለሁ:: በኤርትራ ውስጥ ላለው ችግር ዲሞክራሲያዊ ማሻሻያ ያስፈልገዋል:: ካልሆነ ደግሞ የመንግሥት ለውጥ ከማድረግ ውጪ ሕዝቡ

አማራጭ የለውም:: እዚህ በረሃብና በጥም እየኖረ ያለው ስደተኛ ኤርትራ ውስጥ ያለውን ጭቆናና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሸሽቶ የመጣ ነው:: ዘላቂ መፍትሔው ኤርትራ ውስጥ ያለው ሥርዓት እንዲሻሻል ማድረግ ካልሆነ ደግሞ ከሥልጣን እንዲወርድ ማድረግ ነው:: የአገሪቱ ሕዝብ በየቦታው እየተበተነ ነው ያለው:: እየጠፋ ነው የሚገኘው::

እዚህ በስደት የምታያቸው ከሞትና ከእስራት ያመለጡ ናቸው:: የዓለም ሕዝብ ኤርትራ ውስጥ እየሆነ ያለውን ማወቅ ይኖርበታል:: አሁን ይኼን ነው እየሠራን ያለነው:: የሕግ ምሁሩ ፕሮፌሰር ዮሴፍ ማርጌታ ለተመድ ያቀረቡት የሰብዓዊ መብት ጥሰትም የዚሁ ጥረት አንዱ አካል ነው:: ተመድ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የዓለም አገሮች በኤርትራ መንግሥት ላይ ጠንካራ ዕርምጃ መውሰድ አለባቸው:: ያን ለማድረግ ነው እየተንቀሳቀስን ያለነው::

የኤርትራ አፋሮች

Page 8: Reporter Issue 1201

ገጽ 8|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

በብርሃኑ ፈቃደ

ኢትዮጵያ ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን ለውጭ ባለሀብቶች መስጠት በጀመረች ማግስት ስሟ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተከታታይ እየተነሳ ሲጣል በተለይ ያለፉት ሦስት ዓመታት ይታወሳሉ::

ከ1990ዎቹ መባቻ ጀምሮ በዝቅተኛ ደረጃ የተጀመረው የሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን ለኢንቨስተሮች የመስጠቱ ዕርምጃ፣ ቀስ በቀስ እየሰፋ በመምጣቱ መንግሥትን ሲያስወቅሰው ቆይቷል:: መንግሥት የተከተለውን ፖሊሲ የተቃወሙት ግን አገር በቀል ተቆርቋሪዎች ብቻ ሳይሆኑ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችም ናቸው::

ጥናቶች እንደሚያረጋግጡት፣ የመሬት ገበያ በአፍሪካ የደራው እ.ኤ.አ በ2008 ተከስቶ የነበረውን የምግብ ቀውስ ተከትሎ ነው:: ምግብ ኤክስፖርተር የነበሩት አገሮች በምግብ ምርት ችግር የተመቱበት፣ የምግብ አቅርቦትና ዋጋ የዓለምን ሕዝብ ያስደነገጠበት ያ ጊዜ፣ ለአፍሪካም እጅግ አሳሳቢው ሆኖ ዛሬም ድረስ ቀጥሏል:: ምንም እንኳ በአፍሪካውያኑ ዘንድ ተከስቶ የነበረው ምግብ አመጣሽ የሕዝብ ቁጣ በኢትዮጵያ ሞገደኛነት ባይኖረው፣ ሌላኛው መገለጫው ግን ይታያል::

ቀደም ባሉት ጊዜያት የፖሊሲው ወቃሾች በዋነኛነት የመከራከሪያ ነጥባቸው፣ አገሪቱ ካላት ለግብርና ምቹ ከሆነ መሬት አንጻር ሲታይ ለውጪ ኢንቨስተሮች የሚሰጠው፣ የመሬት ሽሚያን የሚያስመስል አኳኋን አለው የሚለው ነበር:: በወቅቱ የመሬት ሽሚያ የሚለው ወቀሳ ለኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ነው፤ አይደለም የሚለው ጥያቄም የክርክር ማዕከል ነበር:: እ.ኤ.አ 2008 ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ለውጭ ኩባንያዎች ሰፋፊ የእርሻ መሬት በጣም በዝቅተኛ ዋጋ እየሰጠ መሆኑና በዚህም ገበሬዎች ከመሬታቸው እየተፈናቀሉ ለመሆኑ በአሜሪካ የሚገኘው የኦክላንድ ተቋም (Oakland Institute) ሪፖርቱን ይፋ ካደረገ በኋላ የመሬት ሽሚያ ነው፤ አይደለም ክርክሩ ተጧጡፎ መቀጠሉ አልቀረም::

ሰፋፊና ለም የእርሻ መሬቶች ለውጭ ባለሀብቶች እየተሰጡ መሆናቸው፣ የአገር ውስጥና የውጭ ባለሙያዎችን ቱባ ትችት አስከትሏል:: እንደተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ሌሎች የምርምር ተቋማትም የመሬት ሽሚያ አሳሳቢነትን ከማስጠንቀቅ ባሻገር አፍሪካውያኑን ሲተቹ ቆይተዋል:: የዓለም የእርሻና የምግብ ድርጅት (ፋኦ) ዋቢ ይደረጋል::

የኢትዮጵያ መንግሥት ከሦስት ሚሊዮን ሔክታር በላይ ያልተነካ መሬት ለባለሀብቶች እንደሚሰጥ ማሳወቁ ብቻ ሳይሆን መሬቱን ለባለሀብቶች የሚሰጥበት መንገድም ሲያስነቅፈው መታዘብ የተለመደ ክስተት እየሆነ መጥቷል:: መንግሥት ግን የትኛውንም ትችት አይቀበልም::

በኢትዮጵያ ‹‹ኢንቨስት›› ለማድረግ ሰፋፊ ለም የእርሻ መሬቶችን ከወሰዱ ፈርጣማ የውጭ ኩባንያዎች አንዱ ካሩቱሪ ግሎባል የተሰኘው ነው::

ይኸው የህንዳውያን ኩባንያ ኢትዮጵያ እንደገባ በጋምቤላ ብሔራዊ ክልል የተሰጠው መሬት የሚታወስ ነው:: በወቅቱ ከ300 ሺሕ ሔክታር ያላነሰ መሬት እንደተሰጠው መንግሥት ራሱ አስታወቆ ነበር:: ሆኖም ይህ ጉዳይ ያስከተለው የአገር ውስጥና የውጭ ወቀሳን ተከትሎ እንደሆነ ለመገመት በሚቻል መልኩ ኩባንያው በአሁኑ ጊዜ የተፈቀደለት መሬት 100 ሺሕ ሔክታር ወይም 121 ኪሎ ሜትር እንደሆነ ሲነገር ይደመጣል::

የኩባንያው ባለቤቶች ይህ መሬት በምዕራፍ አንድ የኢንቨስትመንት ሒደት የተሰጣቸው እንደሆነ ለተለያዩ ሚዲያዎች ሲገልጹ፣ የተፈቀደላቸው ግን 300 ሺሕ ሔክታር እንደሆነ አስታውቀዋል::

የመሬት ሽሚያ ለኢትዮጵያ ስጋት አይደለምን?

የመሬት ሽሚያን አሁን አሁን ቃሉ እየተቀየረ የመሬት ኢንቨስትመንት፣ የሰፋፊ እርሻዎች የንግድ ኢንቨስትመንት፣ ወዘተ. እየተባለ መለሳለስ ጀምሯል:: የመሬት ሽሚያ የሚለውን ሐረግ በመጠቀም ግንባር ቀደም ከሆኑት ተቋማት አንዱ የዓለም የምግብ ፖሊሲ ምርምር ኢንስቲትዩት (ኢፍፕሪ) ቢሆንም፣ በአሁኑ ጊዜ የሚጠቀምበት ቋንቋ ወደ መሬት ኢንቨስትመንት ተቀይሯል::

የቃሉ መቀያየር ችግሩን እንዳልቀረፈው፣ የስጋትነት መጠኑን እንዳልቀነሰው ከሚገልጹት መካከል ተመራማሪው አቶ ደሳለኝ ራህመቶ አንዱ ናቸው:: በመሬት ጉዳዮች ላይ ካደረጓቸው ጥናቶች አንዱ ለኢንቨስተሮች በሚሰጠው ሰፋፊ የኢትዮጵያ መሬት ላይ ያተኮረ ነው::

ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ለንባብ የቀረበው የአቶ ደሳለኝ ራህመቶ የጥናት ውጤት ተጠቃሽ የሚሆን

ነው:: በእርግጥ የእኚሁ ምሑር ሥራ የእነዚህን የእርሻ ይዞታዎች ለውጭ ኢንቨስተሮች ማስተላለፉን ከአዋጫነቱ ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ዕይታዎች አንጻር ይመለከተዋል::

ሰፋፊ መሬት የሚሰጣቸው የውጭ ኢንቨስተሮች ያመረቱትን ምርት በሙሉ ማለት ይቻላል ወደየአገሮቻቸውና ወደ ዓለም ገበያ የሚልኩ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያን የምግብ ዋስትና የማያረጋግጥ አስጊ አካሄድ እንደሆነ ያስረግጣሉ::

ምርቱ በሙሉ ወደ ውጭ መላኩ ብቻም ሳይሆን በአካባቢና በስነ ምህዳር ላይ ኩባንያዎቹ የሚያደርሱት ጥፋት ተመራማሪውን ያሳስባቸዋል:: በርካታ የደን ይዞታዎች ተጨፍጭፈው፣ ውኃገብ መሬቶችም ተራቁተው ኢንቨስትመንት መካሄዱ፣ ይገኛል ተብሎ ከሚታሰበው ጠቀሜታ አኳያ ሚዛን አይደፋም ይላሉ::

መንግሥት በበኩሉ ሰፋፊ እርሻዎችን ለባለሀብቶቹ በመስጠት አገኛለሁ የሚላቸው የውጭ ምንዛሪ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የሥራ ዕድል ዋናዎቹ ናቸው::

ተመራማሪው አቶ ደሳለኝ እንደሚገልጹት፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እንደሚያረጋግጡት ከሰፋፊ እርሻዎች ኢንቨስትመንት ይገኛል የሚባለው ጥቅም እስካሁን ላም አለኝ በሰማይ፣ ዓይነት ከመሆን አላለፈም:: የሥራ ዕድል ያስገኛሉ መባላቸውም የመነጋገሪያ ርዕስ ጉዳይ ነው:: በአካባቢው ያሉ ዝቅተኛ ገበሬዎችን አፈናቅሎ የሥራ ዕድል ተፈጠረ ማለት ያላዋቂነት ብቻ ሳይሆን ክብረ ነክ እንደሆነ የሚገልጹ አሉ::

ነገር ግን የአቶ ደሳለኝና ሌሎች ጥናቶች

እንዳሳዩት፣ የመንግሥት ዓላማዎች መሳካትን ጥያቄ ውስጥ ሊያስገቡ የሚችሉ አንዳንድ ሁኔታዎች መሬት ላይ መኖራቸውን ነው::

በቅርቡ ለሕዝብ ይፋ የተደረጉ ጥቂት የትላልቅ መሬት ውሎችን ጠቅሰው የጻፉ ምሁራን እንደሚሉት ከሆነ፣ ከላይ የተጠቀሱት ጉዳዮች እነዚሁ ውሎች ላይ አስገዳጅ በሆነ መልኩ አለመስፈራቸውን ነው:: ከዚህ አንጻር እነዚሁ መዛግብት በተለይ ኢንቨስተሩ በአካባቢው ገንዘቡን አፍስሶ ሥራ ሲጀምር ያሟላቸዋል ተብለው የሚጠበቁ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች በውሎቹ ላይ በአስገዳጅነት አለማስፈራቸውን ጠቅሰው ይከራከራሉ:: እንደ አቶ ደሳለኝ ጥናት ግኝት ከሆነ ደግሞ በተለይ የመስክ ምርመራ የተደረገባቸው የጋምቤላ አንዳንድ ቦታዎች በእርግጥም የመሠረተ ልማቱ ፍንጭ ጭርሱኑ ገና እንዳልታየ ያረጋግጣል::

ነገር ግን በዋነኛነት የሚነሳው ጉዳይ ቢኖር የእርሻ መሬቶቹ ተላልፈው እየተሰጡበት ያለው የሊዝ ዋጋ ሁኔታ ነው:: የእርሻ መሬቶች የሊዝ ዋጋን ጨምሮ በጥቅሉ የፕሮጀክቶቹ ምርመራና ማጽደቅ ሥራዎች ቀደም ሲል የሚሠሩት በክልሎች ኢንቨስትመንት ቢሮና የአካባቢ ጥበቃ ትብብር መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ 2010 በኋላ ግን ጉዳዩ ወደ ግብርና ሚኒስቴር እንዲዞር ተወሰነ::

በተለይ አገሪቷ ውስጥ የሚገኙ ከአምስት ሺሕ ሔክታር በላይ የሆኑ መሬቶች በቀጥታ በግብርና ሚኒስቴር ሥር የተቋቋመው ቢሮ ውስጥ ሲገቡ፣ ወዲያውም የእርሻ መሬቶችን በአገሪቱ ወጥ በሆነ ሁኔታ መገመት የሚያስችል የሊዝ ዋጋ መመርያም ይፋ መደረጉ የሚታወስ ነው:: የዕርምጃው ዋነኛ

ምክንያት የእርሻ መሬቶች ለውጭ ኩባንያዎች እየተላለፉበት ያለው ሁኔታ በተለይ የሊዝ ዋጋው ከዓለም አቀፍም ሆነ ከአገር ውስጥ አንጻር የተለያየና ለአንዳንድ ክፍሎች በጣም ዝቅተኛ ሆነው እንደነበር ኃላፊዎቹ በተደጋጋሚ ገልጸዋል::

በአዲስ መልክ ወደ ሥራ የገባው መመርያ የሊዝ ዋጋው ከእርሻ ሁኔታው (ቴክኖሎጂው) ከአዲስ አበባ ያለውን ርቀት ባገናዘበ ሁኔታ የሚወስን እንደሚሆን ይገልጻል:: በዚህ ረገድ ከአዲስ አበባ 700 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ አንድ ቦታ የዝናብ ውኃን ጠንቅቆ ለማዳረስ 111 ብር በሔክታር ይሸጥ ሲል፣ በመስኖ የሚጠቀም ከሆነ 158 ብር በሔክታር ይክፈል ይላል መመርያው:: እንደ አቶ ደሳለኝ ጥናት፣ አዲስ የሊዝ ዋጋ መመርያን ወደ ሥራ በማስገባቱ ረገድ በቅልጥፍና ሥራ ያልተሠራ ከመሆኑ አንጻር ብዙ ኩባንያዎች መሬት እስኪወስዱ ድረስ ተግባራዊ አለመደረጉን መረዳት ይቻላል:: ነገር ግን በአዲሱ መመርያ መሠረትም በተለይም የአሁኑ የሊዝ ዋጋ በኢትዮጵያ በጣም ዝቅተኛ የሚባል ነው የሚሉት እኚሁ ምሁር፣ አገሪቱ እንዴት እንደምትጠቀም ማወቁ ይከብዳል ብለዋል::

በዚህ ረገድ በጋምቤላ ክልል 100 ሺሕ ሔክታር መሬት የያዘውና የህንዱ ካሩቱሪ ኩባንያ በዓመት ሲሰላ የሚያስገኘው 20 ብር በሔክታር መሆኑን መረዳት ይቻላል:: በሌላ በኩል 10 ሺሕ ሔክታር የያዘው ሳዑዲ ስታር 30 ብር፣ ሲምፓር የተባለውና 50 ሺሕ ሔክታር ያለው ሌላው ኩባንያ 143.4 ብር በዓመት ለሔክታር እየከፈለ መሆኑን ከግብርና ሚኒስቴር ይፋ የሆኑ የውል ሰነዶች ያመለክታሉ:: በዚህ ረገድ የሊዝ ዋጋዎቹ በጣም ዝቅተኛ መሆናቸውን ጠቅሰው የሚከራከሩ አዋቂዎች ተበራክተዋል::

በማስረጃና በጥናት የተደገፉ ነቀፌታዎች የሚሰነዘሩበት የኢትዮጵያ መንግሥት፣ ጉዳዩን በብዛት የሚያነካካው ከፖለቲካ ጋር ሲሆን፣ በቅርቡ የግብርና ሚኒስቴር ዴኤታው አቶ ወንድይራድ ማንደፍሮ ለዘመን መጽሔት በሰጡት ቃለ ምልልስ በኢትዮጵያ ካለው 112 ሚሊዮን ሔክታር ውስጥ ለባለሀብቶች ሊሰጥ የተዘጋጀው ከሦስት ሚሊዮን ሔክታር በላይ በመሆኑ የመሬት ሽሚያ (‹‹ወረራ››) አለ ማለት የጠላት ወሬ ነው ብለውታል::

ለባለሀብቶች ተዘጋጅቶ ከሚጠባበቀው መሬት እስካሁን የተሰጠው 400 ሺሕ ሔክታር ገደማ እንደሆነ ሚኒስትር ዴኤታው ቢናገሩም፣ የአቶ ደሳለኝ ጥናት ግን በጋምቤላ ክልል ብቻ 600 ሺሕ ሔክታር መሬት ለአገር ውስጥና ለውጭ ባለሀብቶች እንደተሰጠ ግምቱን ያስቀምጣል::

ከኢትዮጵያ ክልሎች ውስጥ ሰፋፊ የእርሻ መሬቶች ለኢንቨስተሮች የተሰጠባቸው ጋምቤላና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ዋነኞቹ ናቸው:: በተለይ ጋምቤላ የህንዱ ካሩቱሪና የሳዑዲ ስታር ኩባንያዎች ድንግል መሬቷን በሰፊው ከሚቀራመቱባት መካከል አውራዎቹ ናቸው::

የካሩቱሪ ኩባንያ እግሩ የኢትዮጵያን ምድር በረገጠ ማግስት ዓለም አቀፍ ትችት ሲያስተናግድ የቆየ ሲሆን፣ ማስተባበያ ቢሰጥበትም በቅርቡ ከህንድ የወጡ መረጃዎች ለ20 ሺሕ የህንድ ገበሬዎች ከተሰጠው መሬት ሊያከራያቸው ማሰቡን ይፋ አውጥተው ነበር::

ምንም እንኳ የኢትዮጵያ መንግሥት ኩባንያው የተባለውን ጉዳይ የሚያከናውን ከሆነ መሬቱን እንደሚነጥቀው ቢያስጠነቅቅም፣ ባለሙያዎችና ተንታኞች ግን መንግሥት አይዞህ ሳይለው ኩባንያው ይህንን መረጃ ሊሰጥ እንደማይችል በመግለጽ መላምታቸውን ያስቀምጣሉ::

ካሩቱሪ የመጣ ሰሞን

ግዙፉ ካሩቱሪ ወደ ኢትዮጵያ በገባ ሰሞን ዓይኑን በጣለባት ጋምቤላ ክልል፣ ይሠሩ የነበሩ የመንግሥት ኃላፊ፣ በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ኃላፊነት የሚያገለግሉና ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ግለሰብ ሁኔታውን በዝርዝር ለሪፖርተር አስታውቀው ነበር::

ኩባንያው ለክልሉ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ተቆጣጣሪ ለሆነው የግብርናና የአካባቢ ጥበቃ ክፍል የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ስለማካሄዱ የሚገልጽ ሰነድ አላቀረበም:: ሆኖም የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ያላቸውን ግለሰብ አስመጥቶ፣ ‹‹እኚህ ሰው ጥናቱን አካሂደዋል፤›› በማለት አንድ ሆቴል ውስጥ በተገናኙበት ወቅት ከመናገር ውጭ ያቀረቡት ሰነድም ሆነ ማስረጃ እንዳልነበር የወቅቱ ኃላፊ ይናገራሉ::

በዚህ ሁኔታ የተጀመረው የካሩቱሪና የጋምቤላ ክልል ግንኙነት፣ ኩባንያው ከመነሻው ማካሄድ የሚገባውን የተፅዕኖ ግምገማ ማካሄድ አለማካሄድ ሳይረጋገጥና ውጤቱም ሳይጠና ዘሎ የካርታ ጥያቄ እንዳቀረበ የገለጹት ኃላፊው፣ በክልሉ የዚያን ጊዜ አሠራር መሠረት የካርታ ጥያቄ ላይ የሚደርሰው

የ‹‹መሬት ሽሚያ››ና ያስከተለው ስጋት

አቶ ወንድይራድ ማንደፍሮኤልሳቤጥ አታንጋና

ለባለሀብቶች ተዘጋጅቶ ከሚጠባበቀው መሬት እስካሁን የተሰጠው 400 ሺሕ

ሔክታር ገደማ እንደሆነ ሚኒስትር ዴኤታው ቢናገሩም፣ የአቶ ደሳለኝ ጥናት ግን

በጋምቤላ ክልል ብቻ 600 ሺሕ ሔክታር መሬት ለአገር ውስጥና ለውጭ ባለሀብቶች

እንደተሰጠ ግምቱን ያስቀምጣል::

Page 9: Reporter Issue 1201

|ገጽ 9 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

ክፍት የሥራ ቦታአክሲዮን ማኀበራችን ከዚህ በታች ለተጠቀሰው የሥራ መደብ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

1. የሥራ መደብ፡- የምርትና ቴክኒክ ሱፐርቫይዘር

2. ተፈላጊ የት/ደረጃ፡- ከታወቀ ዩኒቨርስቲ/ኮሌጅ በኬሚስትሪ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ

3. የሥራ ልምድ፡- 5 ዓመት በኬሚካል ድርጅት ውስጥ የሠራ ሆኖ ከዚሁ ውስጥ ሁለት ዓመት በምርት ሱፐርቫይዘር የሰራ

4. ብዛት፡- አንድ /1/5. ደመወዝ፡- በአክስዮን ማኀበሩ ስኬል መሠረት6. የመመዝገቢያ ጊዜ፡- ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ

ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚኖሩት 5 ቀናት ውስጥ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃችሁን ፎቶ ኮፒ ከዋናው ጋር በማያያዝ ቢሮ ቁጥር 3 ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

አድራሻ፡- ቃሊቲ ከሜድሮክ ተርሚናል ፊት ለፊት ወደ ውስጥ ገባ ብሎ አልኪድ ሬዝን አክሲዮን ማኀበር የስልክ ቁጥር 0114390247 የፖ.ሣ.ቁ. 1089

የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ የሽያጭ ወኪሎችን መመልመል ይፈልጋል

ተ.ቁ. የሥራ ዓይነት የሥራ ቦታ ተፈላጊ መረጃዎችና መስፈርቶች

1 በረዥም ጊዜ እና

በጠቅላላ የመድን

ዘርፍ በኮሚሽን

የሚሠሩ የሽያጭ

ወኪሎች፣

የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በአዲስ አበባ እና በክልል

ባሉት ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች፣

. ቢያንስ 12ኛ ክፍል ያጠናቀቀ/ች ወይም ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ ያላቸው ሆኖ፣

. የራሳቸው የገቢ ምንጭ ያላቸው፣ ከሽያጭ ወኪልነት ሥራ ጋር የሚቀራረብ የሥራ ልምድ ማስረጃ የሚያቀርቡ፣ ወይንም በጉምሩክ አስተላላፊነት፣ በጉዞ ወኪልነት፣ በትራንስፖርትድርጅቶች አስተባባሪነት ሥራ ላይ የተሰማሩ፣

. ከሥራው ጋር በተዛማጅ ለመሥራት ፍቃደኝነት ያላቸው ድርጅቶች፣

. በተጨማሪም የተመረጡት ዕጩዎች ከብሔራዊ ባንክ የሥራ ፈቃድ ለማውጣት በቅድሚያ፡-

. ለረዥም ጊዜ እና በጠቅላላ የመድን ዘርፍ የሙያ ግዴታ ዋስትና ለመግዛት በቅድሚያ በአጠቃላይ ብር 658.00 /ስድስት መቶ ሃምሳ ስምንት/ በማስያዝ የሚችሉ፣

. ለፈቃድ ማውጫ እና ለሰነድ ማስመርመሪያ ብር 550.00 /አምስት መቶ ሃምሳ/ በቅድሚያ ማስያዝ የሚችሉ፣

. ሥልጠናው ለ30 ሙሉ ቀናት ለመውሰድ ፈቃደኛ የሆኑ፣

o ማሳሰቢያ፡- አመልካቾች በአዲስ አበባ እና በክልል በሚገኙ የድርጅቱ ዲስትሪክቶችና

ቅርንጫፎች ከጥቅምት 20 ቀን እስከ ጥቅምት 25 ቀን 2004 ዓ.ም ብቻ ለአምስት ተከታታይ

ቀናት በሥራ ሰዓት በመገኘት መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

o ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥሮች 0115/512400 የውስጥ መስመር 279/384/230 ወይም 0115/501215 መደወል ይቻላል፡፡

የኢትዮጵያ መድን ድርጅትETHIOPIAN INSURANCE CORPORATION

ካሩቱሪ በወቅቱ የጠየቀው 320 ሺሕ ሔክታር መሬት ከመሰጠቱ በፊት ሊያስተካክላቸው የሚገባው ጉዳዮችንም በዝርዝር ለሪፖርተር አስረድተዋል::

ኩባንያው የጠየቀው መሬት አግድሞሽ 90 ኪሎ ሜትር በርዝመቱ ደግሞ ከ360 ኪሎ ሜትር በላይ የሚዘረጋ በመሆኑ የጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክን ይዞታ 40 በመቶ ያህል የሚነካና የወንዝ ዳርቻን ተከትሎ የተተለመ የመሬት ጥያቄ በመሆኑ የወቅቱ ኃላፊ ውድቅ አድርገውታል:: የ1960ዎቹ የካርታ ይዞታዎች መነሻ ቢደረጉ ደግሞ ካሩቱሪ የጠየቀው መሬት መቶ በመቶ የብሔራዊ ፓርኩ ይዞታ ውስጥ የሚወድቅ እንደሆነም ያረጋግጣሉ::

ኩባንያው የግጦሽ መሬትን በማካተቱም ያንን ማግኘት እንደማይችል፣ የግጦሽ መሬቱ የገበሬዎች ሕልውና የተመሠረተበት፣ ወተትና የከብቱን ሥጋ ሁሉ እንደ ልብ የሚያገኝበት እንደሆነ በመዘርዘር ጥያቄው ውድቅ እንደተደረገ ያስታውሳሉ::

‹‹የግጦሽ መሬት መመናመን ወደ እርስ በርስ ግጭት እንደሚወስድ አስጠነቀቅሁት፤›› የሚሉት የቀድሞው ኃላፊ፣ ‹‹እንዲህ ያለው መሬት ከይዞታህ ውጭ መሆን አለበት፣ አለበለዚያ ካርታ አታገኝም፤›› ብየዋለሁ::

የሱዳን ድንበርተኛ በሆነው የጋምቤላ አካባቢም ዝሆኖች ወቅት ጠብቀው ይመላለሳሉ:: ሕብረተሰቡ የዝሆኖቹን የጉዞ ወቅት ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ይዞታቸውን አክብሮ፣ መንገዳቸውን ከፍቶ ሳይነካቸው በሰላም ይመላለሳሉ:: ዝሆንና ሕዝብ ተከባብረው ይኖራሉ:: የካሩቱሪ ቦታ የዝሆኖቹን መንገድ የሚዘጋ በመሆኑና ለሕብረተሰቡ ሕልውናም ስለሚያሰጋ ይህም ቦታ ከካሩቱሪ ይዞታ ውጭ እንዲሆን በወቅቱ ጥያቄ ተነስቷል::

እንዲህ ዓይነቱን የአይሆንም፣ የአይፈቀድም አቋም ያንጸባረቁት ባለሥልጣን በኩባንያው ሰዎች በይፋ ተዘለፍኩ በማለትም ቅሬታቸውን ገልጸዋል:: ‹‹አንተ ፀረ ልማት ነህ፤›› ተብለው መሰደባቸውንም ያስታውሳሉ:: ‹‹እኔ የሕዝብና የመንግሥት ውክልና ኖሮኝ የተቀመጥሁ፣ ኃላፊነት ያለብኝ መሆኔ እንጂ ከኩባንያውም ሆነ ከሰዎቹ ጋር ምንም አያገናኘኝም፤›› በማለት አሁን ድረስ ያደረባቸውን ቅሬታ በቁጭት ያብላላሉ::

የካሩቱሪ ጉዳይ በዚህ አያበቃም:: ነገሩ እየተካረረ በመሄዱ ለኩባንያው ሲባል የክልሉ አሠራር የተቀየረበትን ሁኔታም ኃላፊው ይናገራሉ:: በክልል የገጠር መሬቶች አጠቃቀም ሥርዓት መሠረት

የትኞቹ መሬቶች፣ ለምን ዓይነት ተግባር መዋል እንዳለባቸው በጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት ሕገ መንግሥት መሠረት ሥልጣን የተሰጠው ለግብርና ቢሮ ቢሆንም፣ የከተማ ልማት ቢሮ በገጠር

መሬቶችም ላይ ሥልጣን እንዲኖረው የተደረገው ለካሩቱሪ ሲባል ነው ይላሉ::

ይህ ብቻ አይደለም እኚህን ባለሥልጣን የሚያሳዝናቸው:: ለኩባንያው ለሰባት ዓመታት ግብር የማይከፍልበት የችሮታ ጊዜ መሰጠቱም ነው:: ወደ ሥራ ከገባ በኋላ አልቻልኩም፤ ከሰርሁ ብሎ አቋርጦ ቢሄድ ያን ሁሉ ደን መንጥሮ፣ ነዋሪዎች

ተፈናቅለው፣ ነዋሪዎች እንዳያርሱት ተደርጎ ባለበት ሁኔታ ለቆ ቢወጣ ጉዳቱ ለጋምቤላ ሕዝብና መንግሥት ነው የሚሉት እኚህ ኃላፊ፣ ‹‹ክልሉ እስከ ሰባት ዓመት አንዲት ሳንቲም አያገኝም፤›› ካሉ በኋላ ለሌላው እንዲህ እንደማይደረግም ያረጋግጣሉ:: ‹‹ሁለት ሔክታር ብትጠይቅ መክፈል ያለብህን ሁሉ ወዲያው ትከፍላለህ፤›› ይላሉ::

ካሩቱሪ ከመምጣቱ በፊት የክልሉ የግብርናና የኢንቨስትመንት ቢሮዎች በጥሩ ትብብር ይሠሩ እንደነበር፣ ግብርና ቢሮ ያላጸደቀው የትኛውም ፕሮጀክት በየትኛውም ተመሳሳይ ኃላፊነት ባለው ባለሥልጣንና ተቋም ዘንድ ተቀባይነት እንደሚያገኝ አስታውሰው፤ ‹‹ካሩቱሪ ሲመጣ ሁሉ ነገር ብልሽትሽቱ ወጥቷል፤›› ኩባንያው ወደ ጋምቤላ ሲገባ በዕልልታ የተቀበለው ገበሬ የለም፣ ይልቁንም ሦስት መንደሮችን የሚያፈናቅል መሆኑ ስጋትን ፈጥሮ ነበር::

ካሩቱሪ የሚወቀሰው በእነዚህ ጉዳዮች ብቻ አይደለም:: ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ሩዝና በቆሎ ለማምረት በማሰብ ለጋምቤላ ክልል ፕሮጀክቱን ቢያቀርብም፣ የስም ለውጥ አደርጋለሁ በሚል ሰበብ (ካሩቱሪ ኃላ/የተ/የግል ማኅበርነቱ ወደ ጋምቤላ ግሪን ባሌ ኃላ/የተ/የግል/ማኀበር)፣ ስልቱን ቀይሮ እንደመጣም ኃላፊው ያስታውሳሉ:: በበቆሎና በሩዝ መካከል የፓልም ተክል እንደሚያለማ የሚገልጽ አንቀጽ ሸጉጦ ወደ ክልሉ መምጣቱ ያሳዝናቸዋል::

ይህንን ሁሉ የተቃወሙት ኃላፊውና ገበሬዎች የሰማቸው አጥተዋል:: ‹‹እንዴት ለም መሬት ላይ የባዮፊውል እንዲያለማ ይፈቀድለታል ብዬ ብናገር ሰሚ አላገኘሁም:: የአገሪቱ ሕግ ግን አይፈቅደውም፤›› ብለዋል:: ካሩቱሪ ተሽቀዳድሞ ወደ ምርት የገባው ይህንኑ የፓልም ተክል በማስቀደም መሆኑ ታውቋል::

በተለይ በጋምቤላ ክልል የተፈናቀለ አንድም ሰው እንደሌለ በመግለጽ አቶ ወንድይራድ ማንደፍሮ ለጋርዲያን ጋዜጣ መናገራቸው ይታወሳል:: ሚኒስትር ዴኤታውን ያነጋገራቸው ጋዜጠኛ ጆን ቫይዳል በካሩቱሪ የእርሻ መሬት ሳቢያ የተፈናቀሉ የአካባቢ ሰዎች ለመኖራቸው በፊልም የተደገፈ ማስረጃ አቅርቧል::

ይህም ብቻ ሳይሆን በቅርቡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የለቀቀው ዜና የጋምቤላ አርሶ አደሮችን ‹‹በፍቃደኝነት›› በአንድ አካባቢ የማስፈር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ይገልጻል::

መንግሥት ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን ለባለሀብቶች የሚሰጠው ሕዝቡን ሳያማክርና ይሁንታ ሳያገኝ ለመሆኑ ማስረጃ እየቀረበበት ባለበት ወቅት፣ የመሠረተ ልማት በቀላሉ ለማቅረብ፣ ለሕዝቡ ተደራሽ ለመሆን በሚሉ በሌሎች አስባቦች ሕዝቡን በአንድ መንደር ማስፈሩ ተዓማኒነት እንዳይኖረው ያደርጉታል::

ይህ የመሬት ሽሚያ ጉዳይ የጋምቤላ ገበሬዎችን ብቻ ሳይሆን መላው አፍሪካውያንን እንደሚያሳስብ የገለጹት የፓን አፍሪካ ገበሬዎች ማኅበራት ፕሬዚዳንቷ ኤልሳቤጥ አታንጋና ናቸው::

ኤልሳቤጥ እንደተናገሩት፣ የገበሬዎች ዋነኛ ሀብት መሬት በመሆኑ ይህንን እየተቃወሙ በውጭ ኩባንያዎች ሕልውናቸው አደጋ እንዳይጋረጥበት የአፍሪካ መሪዎች ያስቡበት ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል:: ተቋማቸው እስካሁን በአፍሪካ ገበሬዎች ላይ የደረሰውን ተፅዕኖ እያጠና እንደሚገኝም አስታውቀዋል::

ለመሆኑ የሽሚያው አሳሳቢነት ትርጉም ያለው መፍትሔ ሊሰጥ እንደሚገባ መላ ከመጠቆሙ ታዋቂ ግለሰቦች መካከልም የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተር አንዱ ናቸው::

ሰውየው አምና እዚህ አዲስ አበባ በመገኘት የአረንጓዴውን አብዮተኛ (ነፍስ መር) ዶክተር ቻርልስ ቦርሎግን ለመዘከር ተገኝተው ነበር:: ለጉዳዩ ጓዳ ሠራሽ ቀላል መፍትሔ ያሉትን ሐሳብ ጠቆም አድርገው ነበር:: ትልልቆቹ ድንበር ተሻጋሪ ኩባንያዎች በተናጠል ያፈረጠሙትን የካፒታል ክንዳቸውን፣ በአነስተኛ ገበሬዎች ጡጫ ማመጣጠን እንደሚቻል ሲገልጹ፣ ‹‹አሥርም፣ ሃያም እያደረጋችሁ ትልቁን መሬት ብትሰጧቸው ትልልቆቹ የሚያመርቱትን ያመርቱላችኋል፤›› በማለት አነስተኞቹን ገበሬዎች በትራክተርና በኮምባይነር ሰበብ አታፈናቅሉ በማለት አስጠንቅቀው ነበር:: ጆሮ የሰጣቸው የለም እንጂ::

በቅርቡ ካሩቱሪ በህንድ አገር የሰጠው መግለጫ በመላው ዓለም መሰራጨቱን ተከትሎ መነጋገሪያ የሆነው የመሬት ሽሚያ በአፍሪካ 22 አገሮችን እንደሚመለከት ሲታወቅ፤ በማዳጋስካር ሰፊ የእርሻ መሬት ለኮርያ ኩባንያ መሰጠቱን ተከትሎ መፈንቅለ መንግሥት እንዳስከተለ ይታወሳል::

ከአዘጋጁ፡- ለዚህ ዘገባ አስራት ሥዩም አስተዋጽኦ አድርጓል::

በዚህ ረገድ በጋምቤላ ክልል 100 ሺሕ ሔክታር መሬት የያዘውና የህንዱ ካሩቱሪ ኩባንያ በዓመት ሲሰላ የሚያስገኘው 20 ብር በሔክታር መሆኑን መረዳት ይቻላል:: በሌላ በኩል 10 ሺሕ ሔክታር የያዘው ሳዑዲ ስታር 30 ብር፣ ሲምፓር የተባለውና 50 ሺሕ ሔክታር ያለው ሌላው ኩባንያ 143.4 ብር በዓመት ለሔክታር

እየከፈለ መሆኑን ከግብርና ሚኒስቴር ይፋ የሆኑ የውል ሰነዶች

ያመለክታሉ::

Page 10: Reporter Issue 1201

ገጽ 10|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

Page 11: Reporter Issue 1201

|ገጽ 11 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

Page 12: Reporter Issue 1201

ገጽ 12|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

Page 13: Reporter Issue 1201

|ገጽ 13 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

WE WORK WITH THE MOST VALUABLE BRAND IN THE WORLD! EXTERNAL ADVERT

Position: Warehouse Coordinator – Addis Ababa

We work with the world’s most cherished trademark, invest in the most sophisticated production system in the world, and employ people who are prepared to work with passion

and focus.

Using your energy, enthusiasm and strong motivational skills, you will be accountable for the following:

To ensure the effective running of the warehouse through coordination of equipments (racking, tools, and forklifts) and people.

Requirements:

• First Degree in Purchasing and Supplies Management /Accounting/ Management and related fieldswith2yearsofrelevantexperiences.

Or• Diploma in Purchasing and Supplies Management /Accounting/ Management and related fieldswith4yearsofrelevantexperiences.

All interested candidates who meet the above criteria and wish to be considered are requested to submit their application with non-returnable comprehensive Curriculum Vitae (CV), and copy of credentials to

East Africa Bottling Share Company, Human Resources Competency.

Closing date for all applications: 9th November 2011

East Africa Bottling Share Company is an equal opportunity employer and is looking for passionate, capable and competent candidates to its team who sustain Company purpose.

Vacancy Announcement Intercontinental Addis Hotel wants to recruit the following positions.

No Position Requirement Experience No of position

Salary

1 Senior Mechanic

Electric Arc Welding, Gas Welding, (Refrigeration, laundry and kitchen)

4 years for Degree/6 years for diploma

1 Negotiable

2 Banquet and Restaurant Manager

Hotel Management

6 years for diploma /4 years for degree

1 Negotiable

3 Electrician Technical school diploma in industrial electricity, Experience on steam generating equipments, laundry and kitchen appliances.

5 Years in hotel, food processing plant or related.

1 Negotiable

N.B.

Applicants are required to send a curriculum Vitae, with

photocopies of non returnable supporting documents within 10

(Ten) days from this announcement Posted on November 1,2011

to P.O.Box 5907 Addis Ababa or submit to Intercontinental Addis

Hotel which is found is Kazanchis.

Vacancy Announcement at Hope University College

Hope University College has the following vacancies. Candidates are invited to apply within 10 working days of this notice to the Formation Office of Hope University College.

1. Executive secretary

Required Qualifications: B.A degree in Secretarial Science or English and four years of working experience as executive secretary.

Desirable: work experience in higher educational institution

2. Secretaries

Required Qualifications: Diploma in secretarial science and two years of working experience as secretary.

Desirable: work experience in higher educational institution Condition of employment: one year contract with a possibility of extension.

Condition of work: full time

Effective date of employment: Immediate

Salary: Negotiable

Place of work: Addis Ababa (applicants are required to move to or live in the vicinity of the University College in Labbu, Jemmu, Lafto, Mekanisa, Hana Maiyam, Ayer Tenna areas).

Applicants should attach their Curriculum vitae, Copies of degrees or diplomas, transcripts and other relevant documents. Hope University College adheres to equal opportunities for all and women are encouraged to apply. Candidates can apply by email or mail to the following addresses.

Hope University College 155 Churchill RoadP.O,Box 28382Addis Abeba, EthiopiaEmail: [email protected] Telephone 01138959238 / 0118959239

Page 14: Reporter Issue 1201

ገጽ 14|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

z ¡ Wü

INVITATION TO BIDAdvertised

Bid No. FA/017/2011Issued By: FARM-Africa EthiopiaPublished Date November 2, 2011Bid Category Computers, Printers, Communication, Camping and field equipment

1. FARM-Africa now invites sealed bids from eligible bidders to purchase desktop and Laptop computers, Printers, camping and field equipment to its different projects.

2. Bidders should abide with the rules & regulation of value added tax (VAT) and others specified by the government of Ethiopia. Failure to do will result in automatic rejection form the bid.

3. All bids must be accompanied by a 1% bid security of total bid amount in the form of unconditional Bank Guarantee or CPO and shall remain valid for 90 (ninety) days. Bid bond in any other form shall not acceptable.

4. Bids shall be valid for a period of Ninety (90) days after Bid opening date. 5. A complete set of bidding documents, specification and no of items to be purchased, can

be collected by interested bidders on the submission of a written application and copies of necessary renewed license to FARM-Africa Co.

6. Bids shall only be submitted in wax-sealed, envelope otherwise, the bid will be disqualified. 7. Bids must be delivered to the FARM-Africa Office on or before 17 November 2011.8. Bids will be opened in the presence of the bidders or their representatives at 10:30 A.M.

on 18 November 2011 at the FARM-Africa office. 9. Failure to comply any of the conditions above shall result in automatic rejection of the

bid. 10. The FARM-Africa reserves the right to reject all or part of the bid. 11. Specify in your envelope to which items you participated. 12. Supplier should state the delivery time. 13. Sample may be requested from the winner supplier.

FARM-Africa in Ethiopia located near to IBEX Hotelin front of Saudi Arabia Embassy,Tel. 0114-406514 or 0911 454644

Addis Ababa, Ethiopia

ወይ ጊዜ?ዛሬ ከፒያሳ አዲሱ ገበያ ነን። በተራ የተደረደሩት ታክሲዎች እንደ አቋቋም ሥነ ሥርዓታቸው

ሁሉ ተሳፋሪውንም በተራ ይጭናሉ። ጭር ባለው የቀትር ጊዜማ ሕዝበ አዳም የት እንደገባ ግራ እስኪገባ ድረስ አይታይም። ታክሲዎች ባዶ ሆነው ወያሎች በትጋት ሲጣሩ ሲታዩ ታታሪ ሠራተኛ የሆኑ ይመስላል። እውነት ብንሠራ ነው እንዴ መዋጮና ብድር ስንጠይቅ የምንውለው? ሆድ ይፍጀው አለ የአገሬ ሰው። ‹‹ለመንቀሳቀስ ሁለት ሰው ብቻ ነው የጎደለው›› ብሎ አንዱ ወያላ ጎትቶ አስገባኝ። ከአሁን አሁን ሞልተን ልንሄድ ነው ብዬ ብጠብቅ ጭራሽ ገብተው የነበሩት ወርደው መሄድ ጀመሩ። ለካ ታክሲዋ የማታውቀን እኔንና ሁለት ተሳፋሪዎችን ብቻ ነበር። ‹‹ምን አለበት ትንሽ ብትቆዩልኝ?›› ይላል ወያላው ተናዶባቸው። ‹‹አንተ አትሞላምና ተጎልተን እንዋል?›› ብለው እያሾፉበት ሄዱ። አንዱ ባንዱ ላይ እያላገጠ ዘመናት ሲነጉዱ ትዝም አይለን::

‹‹ምን ይሻላል?›› አሉ ቆይተው የገቡ ተሳፋሪዎች። ‹‹ብንወርድ ሌላ የሚጭን ታክሲ የለም፤ ብንቀመጥ ከዓመት በኋላም የሚሞላ አይመስል፤›› አለ አንደኛው:: ‹‹ሸወደን እኮ እባክህ?›› ይላል ሌላው ተሳፋሪ። ‹‹ምን ታደርገዋለህ አስመሳይ ብቻ እኮ ነው የተሰበሰበው፤ በቃ ማስመሰል፤ የሞላ ማስመሰል፣ የተሠራ ማስመሰል፤ ያልተራብን ማስመሰል፤ ታማኝ መምሰል፤ በማስመሰል አለቅን እኮ እባካችሁ?›› ብሎ በብስጭት እጆቹን እያወናጨፈ ያወራል። ወዲያው ስልኩ ጠራችና አነሳት። ‹‹አቤት? ወዬ ሆዴ እንደምን ዋልሽ? ይገርምሻል ደርሻለሁ፤ ውጭ በቃ አሁን፤ እውነት እውነት ደርሻለሁ፤›› እያለ በሌባ ጣቱ ያልደረሰበትን ቦታ በማስመሰል ይጠቁማል። ስለማስመሰል እየነገረን እሱ ራሱ አስመሳይ መሆኑን ሲያሳይ ትንሽ አልከበደውም:: ለነገሩ ለምን ይከብደዋል? ከማን የተማረውን እውነት ሊያሳየን ነበር? አገር ምድሩን ቅጥፈት ሞልቶት እውነተኝነትና ታማኝነት ምን ይፈይዳሉ የተባለ ይመስላል::

ታክሲያችን እንደምንም ሞልታ መንቀሳቀስ ጀመርን። ወያላው ብዙ የጮኸበትን ጉሮሮውን ለማራስ ጀላቲ መምጠጥ እንዳማረው ጮክ ብሎ ለሾፌሩ ነገረው። ‹‹ግዛ ለምን እኔን ትጠይቀኛለህ? ታዲያ የበሶ ግዛ ለሰውነትህ ተስማሚ ይሆንልሃል፤›› ሲለው ፈገግ አልን። ‹‹እውነቴን እኮ ነው እየከሳብኝ ምን ይሻለኛል?›› እያለ ማፌዙን ሲቀጥል፣ አንድ ጎልማሳ ተቀበለውና፣ ‹‹ራሱ ሰው ሳይሆን ለሰው ሲጮህ ሲውል እንዴት አይከሳ?›› አይሉት መሰላችሁ? ወዲያው የሁሉም ፊት ኮስተር እያለ ደህና ተሟሙቆ የነበረውን የታክሲያችንን ጨዋታ አደፈረሰው። አንዳንዱ ሥራው እሳት ላይ ውኃ መድፋት ብቻ ነው ልበል? የሞቀ ነገር ማቀዝቀዝ ብቻ። ሁሉም በየሆዱ የሚያኝከውን ነገር ረገብ ለማድረግ በታክሲዋ ውስጥ ጨዋታ የፈለገ ይመስላል። ወዲያው ወያላችን የበሶ ጀላቲ እየመጠጠ ሲመጣ አየነው:: እውነት መስሎት ይሆን የበሶ ሲባል? ስንቱ የዋህ ይሆን በአሿፊ መካሪዎች ጉድ የሚሆነው? በፍየል ዘመን በግ የሚሆኑ ሲያጋጥሟችሁ አያሳዝኑም?

‹‹ይገርማል ዛሬ ደግሞ ጀላቲ ከሚመጥ ወያላ ጋር ነው የምንሄደው፤›› አለ አንድ ወጣት። ‹‹ምን ያድርግ ታዲያ እንደዚህ አንዳንዴ ምሳውን እያሰበ ቢውል? መቼም እንደ መሬት ሊዝ አዋጅ ዓመታዊ ምሳን አስቦ የመዋያ ቀን እስኪታወጅ መጠበቅ አለበት?›› ብሎ ዞር አለ ሌላው። ወዲያው አንዱ ተሳፋሪ ከተቀመጠበት ተነሳና ‹‹መሬት? መሬት ምን ሆነ? መሬት ምን ሆነ?›› ብሎ አፈጠጠብን። ‹‹ኧረ ስለ መሬት አልተወራም ምን ሆነሃል? እኛ ያልነው እንደ መሬት ሊዝ አዋጅ አንድ ቀን ምግብን አስቦ የመዋያ ቀን ሊታወጅ ይችላል ነው። ምን ሆነሃል ኧረ እባክህ ቁጭ በል፤›› ብለው አጠገቡ የተቀመጡት ሰዎች አረጋጉትና አስቀመጡት። ወያላው በእሱ ጀላቲ ይህ ሁሉ እንደ ተከሰተ ሲያይ ሌላ ሳይከተል በሚል ስጋት በመስኮቱ ወረወረው። ‹‹እየሠሩ መብላት መከራ!›› አለና ሒሳቡን መሰብሰብ ጀመረ።

ሒሳቡን ተቀብሎ ሲጨርስ ለመልስ ይዞር ጀመር። ከመዳፉ የሳንቲም ፎቅ ላይ እያነሳ ይሰጣል። የሳንቲሙ ፎቅ አሠራር ባለሀብት አስመስሎት ነው መሰል ከሚሰጠው መልስ ላይ አስር ሃያ ሳንቲም እየቆረጠ ኪሱ ውስጥ ይከታል። ይህንን አጠገቤ የተቀመጠችው ወጣትና እኔ አስተውለናል። በኑሮ፣ በመሬት፣ በትዳር፣ በግብር፣ በልጆች የናወዙ ተሳፋሪዎች የሚሰጣቸውን የሳንቲም መልስ አስተውለው አይቀበሉም። ይህ ለወያላው ‹‹ኪራይ መሰብሰብ›› መንገድ ከፍቶለታል። ድንገት ጋቢና የተቀመጠች ተሳፋሪ የሰጣትን መልስ ቆጥራ ‹‹የታክሲ ታሪፍ ጨመረ እንዴ?›› ብላ ሾፌሩን ጠየቀችው። ሾፌሩ እያሳቀ ‹‹መልሱ አንሶሽ ከሆነ ወያላው ለራሱ የተጨማሪ እሴት ታክስ እየሰበሰበ ይሆናል፤›› ሲላት ሳቅን::

በሐሳብ ባህር ይዋኝ የነበረው ተሳፋሪ ‹‹ምን? እስኪ ድምፅ ስጠው ሾፌር። እንዲያው ምን ይሻላል?›› ማለት ጀመረ። ሾፌሩ ግራ ገብቶት ‹‹የምን ድምፅ ነው የምሰጠው?›› ብሎ ተሳፋሪውን ቃኘት አድርጎ መሪውን ጠበቅ አደረገ። ‹‹ቀልዱን ተውና መልሴን፤›› አለች ጠንቃቃዋ ሒሳብ አወራራጅ። ስንቱ እንዳንቺ ቢሆን የት ይደርስ ነበር? እያልኩ ሁኔታውን እከታተላለሁ። ወዲያው ወያላው፣ ‹‹ኧረ ልሰጥሽ ነው:: ምን ቡራ ከረዩ ያስብልሻል?›› ብሎ መልሷን ሰጣት። ይኼኔ ሁሉም መልሱን መቁጠር ጀመረ። ‹‹አንዳንዱ ሳይኖረውም ቢሆን አውጥቶ የሞት ፍርድ የተፈረደበትን ወገኑን ያድናል:: ይኼ የሰው ኪስ ገብቶ ይዘርፋል፤›› አለችን አጠገቤ የተቀመጠችው ቆንጆ ወጣት። ‹‹አንዳንዶች አግኝተው ቢያጡም መስጠት ይወዳሉ። መልሰው እንደሚያገኙት በማሰብ ነው ታዲያ። ይኼ ግን ፊደል ያልቆጠረ ስለሆነ ይሆናል፤›› አላት ከኋላ የተቀመጠው ተሳፋሪ። ተጀመረ አትሉም?

መውረጃዬን ትቼ የመነጋገሪያ መድረኩን በፈጠረችልኝ ቆንጆ ምክንያት ለሁለተኛ ጊዜ ሒሳብ ከፈልኩ። እቀጥላለሁ ብዬ። ‹‹እንዲህ ዓይነቱን ነበር አባሮ መጨረስ፤›› አለችኝ ዞር ብላ እያየችኝ። አቤት መልክ? ‹‹ግን ይኼን ሁሉ አባረሽ ትጨርሻለሽ ብለሽ ነው?›› አልኳት:: ‹‹መጨረስ እንኳን አያቅትም፤ ግን ብቻህን ትጨርሳለህ ወይ ነው ጥያቄው። እንኳን እኛ መንግሥት ራሱ ማባረር ጀምሯል አሉ፤›› ስትለኝ፣ ‹‹እነ ማንን?›› አልኳት:: ‹‹አይ? የሚጠየቅና የማይጠየቅ አታውቅም እንዴ?›› ስትለኝ በጥያቄዬ አፍሬ ዝም አልኩ። ስንቶቻችን እንሆን የሚጠየቀውን ከማይጠየቀው የምንለይ? የሚጠይቁትን የማያውቁ ብዙዎች እስረኛ ዘመዳቸውን አልጠይቅ እያሉ ሆድ ተባብሰዋል ይባላል።

ታክሲያችን የትራፊክ መብራት ይዟት ቆማለች። በእግረኛው መንገድ ላይ በሽቅርቅር አለባበስ የምትወዛወዝ የምትመስል ወጣት ላይ አንዷ የልብስ እጣቢ ደፍታባት ድብድብ ቀረሽ ንትርክ ተጀምሯል:: ይኼን እያዩ አንድ ተሳፋሪ፣ ‹‹ወንዶቻችን ተመልከቱ፤ ድሮ በእኛ ጊዜ ሴት ልጅ እንኳን እንዲህ ልትለብስ ቡና ስታፈላ እግሯን ቆልፋ፣ ስትስቅ አፏን ይዛ ነው። ዕድሜ የማያሳየኝ የለም ይኼው ዛሬ ይኼ ሁሉ ቀርቶ ስትደባደብ እያየሁ ነው፤›› አሉ። ‹‹አባባ ጊዜ እኮ ይቀየራል። የእናንተ ጊዜ የእናንተ ነበር፤ የእኛ ጊዜ ደግሞ የእኛ ነው፤›› አለቻቸው አጠገቤ የተቀመጠችው ቆንጆ። ‹‹ማን ነው የእናንተ ብቻ ያደረገው እ? በሊዝ ነው የገዛችሁት እ? ንገሪኛ? እኛ እየኖርን አይደለም? ጊዜ ለኖረበት ሁሉ ነው። የዛሬን ጊዜ ግብር ታውቂዋለሽ። ታዲያ ስተከፍይ መቼም የእኛ ጊዜ ስለሆነ ነው ብለሽ ነው? አይደለም። እሴት ስታፈርሱ ግን የእኛ ጊዜ ስለሆነ ነው ትያለሽ አዳሜ፤›› ብለው ወራጅ አለ አሉ። እኚህ ሰው እንዲህ ለመናገር የደፈሩት መውረጃቸውን አውቀው ስለነበር ነው? ዲሞክራሲ ያጎናጸፈን ተናግሮ መሮጥን ከሆነ የዲሞክራሲው ትውልድ ውኃ በላው አትሉኝም? ወይስ ሰውዬው ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀም በመሞከራቸው የተለመደው ዱላ ይከተላል ብለው ነው? ይገርማል::

ነገራችን ሁሉ ‹‹የዛፍ ላይ እንቅልፍ›› ከሆነ ውሎ አድሯል። አንዳንዴ ዝምታ የብሶት አውድማችን ይሆንና ይሰነብታል። አንዳንዴ እንዲህ በተገናኘን ቁጥር እንተነፍሰዋለን። በየታክሲው፣ በየካፍቴሪያው፣ በየጥጋጥጉ የአገሬ ሰው የተሰማውን አሽሞንሙኖና አለሳልሶ ማቅረብ ይችልበታል። ምን ቢያለሳልሰው አሁን አሁን ግን ጭራሽ ከመሰማት ያራቀው ይመስላል። ‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› ያለው ጠቢቡ ሰባኪ ትዝ አለኝ። ለመጮህ ጊዜ አለው፣ ለመሰማት ጊዜ አለው፣ ለማስመሰል ጊዜ አለው፣ ኪራይ ለመሰብሰብ ጊዜ አለው፣ ለመታሰር ጊዜ አለው፣ ለመፈታት ጊዜ አለው፣ ዓባይ ተገድቦ ለማየት ጊዜ አለው፣ እስኪገደብ ድረስ ለማዋጣት ጊዜ አለው፣ ጀላቲ እንደ ምሳ ለመምጠጥ ጊዜ አለው፣ ለምኑም ለምኑም ጊዜ አለው:: ባይባልም እንኳ እንደ ተባለ እያልኩ። ብቻ ጊዜ ሲደርስ ሁሉም ነገር መልሱን ያገኛል ማለቱ ይሻላል::

ጉዟችን እየተገባደደ ነው። ተሳፋሪዎች ወደየጉዳያቸው ለመሮጥ ያሰፈሰፉ ይመስላሉ:: ታክሲ ውስጥ ለመሆን ጊዜ አለው፣ ለመውረድ ጊዜ አለው የሚሉ ይመስላል። ቀና ብዬ የተሰቀለውን ጥቅስ አየሁ። ‹‹የጊዜ እንጂ የሰው ጀግና የለውም›› ይላል። ይቺም ጥቅስ ለመውረድና ለመሰቀል ጊዜ እንዳላት የምታውቅም አትመስልም። ነገሮች ጊዜ በሚባለው ስውር ነገር ውስጥ ሲመላለሱ የሁላችንም ተስፋ፣ ምኞት፣ አደራና አለኝታ ጊዜ ይሆናል ማለት ነው:: ወያላው ‹‹መጨረሻ›› ብሎ እንደለመደው ወደ ጀላቲ መሸጫ ኪዮስክ ሲሮጥ ሁላችንም በሐዘኔታ አየነው። ለሐዘንም ጊዜ አለው ይባል? ወይስ እንዲያው በጠቅላላው ለሁሉም ጊዜውን ይጠብቅለታል ብለን እንሰነባበት? ምን ይደረግ ተንጠልጥለን ያለነው እኮ ጊዜ እስከፈቀደልን ድረስ ነው? መልካም ጉዞ!

Invitation to bid for sale

of used Trucks

Total Ethiopia S.Co. is interested to dispose 2 pcs of used IVECO Trucks through auction. Therefore, any interested bidders are invited to visit the Trucks & can purchase bid document against non refundable payment of birr 100.00 from Purchasing Division.

1. Bid must be accompained by a bid bond 10% of the total offered value in CPO cheque.

2. Interested bidders can visit the vehicle during working days from 8:00 a.m to 5:00 p.m at Head office effective November 2, 2011 till November 7, 2011.

3. Bid shall be closed on November 07, 2011 at 2:00 P.M.4. Bid price should include VAT and VAT should be stated as

separately line item. 5. Title transfer fee of the Trucks will be covered by the bidder. 6. The Trucks will be sold at the existing condition. 7. The winner has to collect the Trucks with in three days upon

payment of full amount of the bid price. 8. Bid document must be sealed in envelope and be addressed to Total Ethiopia S.C Purchasing Division 9. Total Ethiopia S.Co reserves the right to reject partial or all part

of the bid.

Page 15: Reporter Issue 1201

|ገጽ 15 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

Call for ConsultancyADV is a national NGO engaged in promoting the improvement of the plight of disadvantaged members of society in different parts of Ethiopia. As part of its overall programme, and with a financial support from the EuropeanCommission Civil Society Fund ADV and its partners WCDO, EBBA, and CEDAC is implementing a project entitled “Enhancing the organizational performance of women focused organizations”,contractref.FED/2009/217-688intheperiod30Nov.2009to30thNovember,2011.

The project has the overall objective of contributing to the advancement, development and empowerment of women and thereby enhancing their participationindevelopmentinfivesub-citiesofAddisAbabaCityAdministration.

Now, the implementation period almost at end ADV has decided to commission and engage an external consultant to evaluate the overall performance ofimplementation with the aim to contribute to strengthening accountability to key stakeholders and the internal learning of ADV with regard to performances in programme implementation, generating lessons learnt and assuring result orientation.

Thus, ADV would like to invites eligible consultants/firms to conduct theevaluation. Interested consultants can collect the TOR from ADV officeimmediatelyaftertheannouncementispostedinthenewspaperduringofficehours fromMonday toFridayandshouldsubmit their technicalandfinancialproposals to thesameoffice inaseparatelysealedenvelopewithin10daysfromthedateofannouncement.PleasenotethatthefinalevaluationshalltakeplaceinDecember2011andthefinalevaluationreportisexpectedattheendofJanuary2012.

AddressAddis Development VisionNefasilk Lafto, Wereda 2(in front of Wereda 2 Youth sport and entertainment: Mekanissa)P.o.Box 12017, Addis Ababa, Ethiopia

አያት አክሲዮን ማኀበር ለቀጣይ 5 ወራት 30,000 (ሠላሣ ሺህ) ሜትር ኩብ ንፁህ የወንዝ አሸዋ (River sand) ለመግዛት አቅራቢዎችን ይጋብዛል::

ስለዚህ ከላይ ከተጠቀሰው መጠን ውስጥ 70% (21,000 ሜትር ኩብ) አሸዋ ሲ.ኤም.ሲ. ሚካኤል ቤተክርስቲያን ጀርባ - ሲሲኢ ግቢ ውስጥ ካለው የአያት ባችንግ ኘላንት እንዲሁም ቀሪው 30% (9,000 ሜትር ኩብ) አሸዋ አያት መንደር የግንባታ ሳይት ለማቅረብ የምትፈልጉና ሕጋዊ ደረሰኝ የምትሰጡ አቅራቢዎች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ዋጋችሁን በታሸገ ፖስታ ማቅረብ የምትችሉ መሆናችሁን እናስታውቃለን::

አያት አክሲዮን ማኀበርዋና ሥራ አስፈፃሚ ቢሮ

ሲሲኢ ቢሮ ስልክ ቁጥር 0116463448 / 0911475326

አዲስ አበባ::

የአሸዋ ግዥ ማስታወቂያ

(ጥንቅር- ብሩክ ቸርነት)

ጨረታ እና ንብረት

ግዥ

ጨረታውን ያወጣው መሰሪያ ቤት፡- በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግሥት የግብርና ቢሮ:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የላቦራቶሪ መሣሪያዎች ቁሳቁሶች፣ ፈርኒቸሮች (ረጃጅም ጠረጴዛዎች፣ የብረት መደርደሪያዎች በርጩማዎች) ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 046 220 08 66 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መሰሪያ ቤት፡- የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የቢሮ ፈርኒቸር፣ የምግብ ማብሰያና ማዘጋጃ ዕቃዎች፣ የኢኒፎርሚሽን ቴክኖሎጂ ዕቃዎች፣ የህትመት መሣሪያዎች:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 645 36 98 የውስጥ መስመር 231/205/271 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መሰሪያ ቤት፡- የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽ/ቤት:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የቴራዞ ምርቶች (የቴራዞ ዊንዶ ሲል፣ ቴራዞ ትሬድ፣ ቴራዞ ራይዘር) :: ጨረታው የሚከፈተው፡- ሕዳር 10 ቀን 2004 ዓ.ም.:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011-371-23-66/80 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መሰሪያ ቤት፡- የኢትዮጵያ እህል ንግድ ድርጅት:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- ተንቀሳቃሽ ሚዛን:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ጥቅምት 29 ቀን 2004 ዓ.ም.:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 466 47 43 ወይም 011 4 65 31 66 ይደውሉ::

-----------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መሰሪያ ቤት፡- በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የፋይናንስ ግዥና ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የስራ ሂደት:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶች፣ የሰራተኞች የደንብ ልብስ፣ አላቂ የንጽህና መጠበቂያ እና የጽዳት ዕቃዎች:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ሕዳር 4 ቀን 2004 ዓ.ም:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 830 20 49 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መሰሪያ ቤት፡- የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የተለያዩ ዓይነት መጠን ያላቸውን ጎማዎች:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ሕዳር 12 ቀን 2004 ዓ.ም:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 665 05 82 ወይም 011 665 06 93 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መሰሪያ ቤት፡- የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን::

በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የጽ/መሣሪያዎች፣ የጽዳት እቃዎች፣ የተሽከርካሪ ጎማዎች:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 466 72 68 ወይም 011 466 72 86 ይደውሉ::

------------------------------------

ሽያጭጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡-

የኦሮሚያ ደንና ዱር እንሰሳት ድርጅት:: በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ የሚፈልገው፡- የቁም ደን:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 840 24 64 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የስኳር ኮርፖሬሽን ግብይት ዘርፍ:: በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ የሚፈልገው፡- ባለ 30 ኪሎ የታሸገ ከረሜላ:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ጥቅምት 30 ቀን 2004 ዓ.ም:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 840 24 64 ይደውሉ::

------------------------------------

ኮንስትራክሽን ጨረታውን ያወጣው መሰሪያ ቤት፡

- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዳግማዊ ምኒልክ ሪፈራል ሆስፒታል:: በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት የሚፈልገው፡- የህንጻ

ግንባታ:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ሕዳር 20 ቀን 2004 ዓ.ም.:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0113 71 20 89 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መሰሪያ ቤት፡- የኢትዮጵያ እህል ንግድ ድርጅት:: በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት የሚፈልገው፡- የመጋዘን:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ሕዳር 8 ቀን 2004 ዓ.ም.:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 4666 47 43 ወይም 011 416 11 38 ይደውሉ::

------------------------------------

ኪራይ

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን:: በጨረታ አወዳድሮ ማከራየት የሚፈልገው፡- ለቢሮ፣ ለካፌና ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችን:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ሕዳር 20 ቀን 2004 ዓ.ም.:: ለበለጠ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 046 220 33 19 ወይም 046 220 22 09 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የኦሮሚያ አደጋ መከላከያና ዝግጁነት ኮሚሽን:: በጨረታ አወዳድሮ ማከራየት የሚፈልገው፡- ከ6-9 (Log bez) መኪናዎች:: ለበለጠ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 011 442 77 70 ይደውሉ::

------------------------------------

Page 16: Reporter Issue 1201

ገጽ 16|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

Re-Advertisement

Invitation for Bid for the Financial Audit ofDrought Intervention Ethiopia 2011

ECHO/ETH/BUD/2011/91001

Cordaid is implementing a 6 month ECHO funded program on Drought InterventionEthiopia2011inBoranaandGujjizonesthrough3partner

organizations

Afinancialauditisplannedfortheprogramperiod1April2011till30September2011

Cordaidherebyinvitesinterestedfirms/companiestobidfortheauditoftheprogram. The terms of reference and other related materials can be collected

fromCordaidofficeinEthiopiafrom3rdNovember2011.Deadlineforsubmission of bid is 9thNovember2011at5.00p.m.

AllbidsaretobesubmittedinhardcopyatourEthiopiaofficeduringofficial

workinghours(8.00am-5.00pm)

“CORDAID DIE AUDIT BID” CordaidFieldOffice

Haile G/Selassie Road(near lem hotel)

Bisrat Building, 1st FloorRoom Nr. 9

POBox27638/1000,AddisAbabaTel.+251116632450

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ

የኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ባሉት ክፍት የሥራ መደቦች

አመልካቾችን አወዳድሮ በፈተና ብልጫ ያመጡትን ለመቅጠር

ረቡዕ ሐምሌ 27/2003 ዓ/ም በሪፖርተር ጋዜጣ ባወጣው የቅጥር

ማስታወቂያ መሠረት ከዚህ በታች ለተገለጹት ሁለት የሥራ

መደቦች ማለትም፡-

1. ለንዑስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኦዲተር፡- ክፍት የሥራ መደብ ብዛት

50

2. ለቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጁኒየር አይቲ ኤክስፐርት፡- ክፍት የሥራ

መደብ ብዛት 13

ቀርባችሁ የተመዘገባችሁና የፈተና ጥሪውን በመከታተል ላይ

ለምትገኙ ተመዝጋቢዎች በሙሉ ፈተና የሚሰጠው ሰኞ ጥቅምት

27 ቀን 2004 ዓ/ም ስለሆነ በዕለቱ ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ማንነታችሁን

የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ላይ እንድትገኙ ጥሪያችንን

እናስተላልፋለን፡፡

ለበለጠ መረጃ፡- 046 220 20 53

ተቋሙ!

CCRDAየክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ማህበራት ህብረት 12 (አስራ ሁለት) SUZUKI ወይም YAMAHA ሞተር ሳይክሎችን ለዚሁ የተዘጋጀውን መስፈርት ከሚያሟላ ድርጅት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡በዚህ ጨረታ ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቶች፡-

1. አግባብነት ያለው የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፣የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ በገንዘብ ሚኒስቴር በአቅራቢነት የተመዘገቡ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣

2. የጨረታ ሰነዱ Áህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ቃሊቲ መንገድ የአሽከርካሪዎችና መካኒኮች ማሰልጠኛ ፊት ለፊት በሚገኘው የክርስቲያን በጎ አድራጎትና የልማት ማህበራት ህብረት አስተዳደርና ፋይናንስ ክፍል 102 ቁጥር በመቅረብ ብር 50.00 /ሃምሳ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡

3. ለጨረታ ማስከበሪያ ከሚሰጡት ዋጋ 2% በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲፒኦ ወይም ቢድ ቦንድ ማስያዝ አለባቸው፡፡

4. የሚወዳደሩበትን ሰነድ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ እስከ ህዳር 4 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ከላይ በተገለፀው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

5. በጨረታ ሰነዳቸው ላይ የሞተር ሳይክል ጨረታ ብለው መጻፍ ይኖርባቸዋል፡፡

ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ህዳር 12 ቀን 2004 ዓ.ም በክርስቲያን በጎ አድራጎትና የልማት ማህበራት ህብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከቀኑ በ4፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡

የክርስቲያን በጎ አድራጎትና የልማት ማህበራት ህብረት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ለተጨማሪ መረጃ የስልክ ቁጥር 0114 39 33 32/0114 39 06 52 ይጠቀሙ፡፡

አድራሻችን- የክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ማህበራት ህብረት ደብረዘይት መንገድ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ከአሽከርካሪዎችና መካኒኮች ማሰልጠኛ ተቋም ፊት ለፊት

የጨረታ ማስታወቂያኩባንያችን የካሣ ክፍያ ፈጽሞ የተረከባቸውን ተሽከርካሪዎች፣ የተሽከርካሪ አካላት እና ሌሎችን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ተሽከርካሪዎቹንና የተሽከርካሪ አካላትን መግዛት የሚፈልጉ ሁሉ ቃሊቲ ኢትዮ

ኒፖን ጋራዥ ፊት ለፊትና ቃሊቲ ቆርኪ ፋብሪካ ጀርባ በሚገኘው የኩባንያችን ሪከቨሪዎች በመገኘትና በማየት የሚገዙበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ ህዳር 1 ቀን 2004 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ ደንበል ህንፃ 2ኛ ፎቅ በሚገኘው የካሣ መምሪያ ለዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ገቢ በማድረግ መጫረት ይችላሉ፡፡

ጨረታው ህዳር 2 ቀን 2004 ዓ.ም. ከቀኑ 4፡00 ሰዓት በኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት ተጫራቾች ወይንም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ይከፈታል፡፡

ሌሎች ተጫራቾች ባቀረቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት የተከለከለ ነው፡፡ ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዕቃ የመነሻ ዋጋውን 10% (አስር በመቶ) በባንክ

ክፍያ ማዘዣ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ሆኖም የጨረታ ማስከበሪያው ከብር 5,000.00 (አምስት ሺህ) ማነስ የለበትም፡፡

ከቀረጥ ነፃ ከሆኑት ተሽከርካሪዎች በስተቀር በሌሎች ተሽከርካሪዎችና አካላት ከጨረታው በፊት ዕዳዎች ቢኖሩ በኩባንያው ይሸፈናል፡፡ በጨረታው ለተካተቱ ንብረቶች ከጨረታው በኋላ ያሉትን ማናቸውም ወጪዎች ገዥው ሙሉ በሙሉ ይሸፍናል፡፡

የጨረታው አሸናፊዎች ያሸነፉበት ዋጋ ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 15% (አስራ አምስት በመቶ) በተጨማሪነት የከፈላሉ፡፡

አሸናፊዎች የጨረታው ውጤት ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ እስከ ህዳር 12 ቀን 2004 ዓ.ም ድረስ ክፍያ ፈጽመው ንብረቶቹን ካልተረከቡ የጨረታው ውጤት የሚሰረዝ ሆኖ ከላይ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ገንዘብ ለኩባንያው ገቢ ይደረጋል፡፡

ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ.)

( 552- 81-95/96 ፋክስ 552- 81-93 285

የጨረታ ማስታወቂያ

Page 17: Reporter Issue 1201

|ገጽ 17 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

Page 18: Reporter Issue 1201

ገጽ 18|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

Page 19: Reporter Issue 1201

|ገጽ 19 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

ገራገርቴዲ

በዮናስ አበበ

ከቶ አይወስነውም ዘር ሃይማኖት ቦታ

የአምላክ ፈቃድ ገብቶት ከስግብግብነት ልቡ ከተፈታ፣

ኢየሱስ የከፈለው ነፍሱን ለነፍሳችን

ክብሩን ሲያሳየን ነው የውድ ሕይወታችን፣

ቴዲ

ገብቶሀል ነገሩ የነፍስ ምሥጢር ፍቺ

እንደማይገዛ በገንዘብ በሥልጣን ወይም ባማላጅ

ስለዚህ ታደከው ነፍሱን ሳያሰጥ ሊወስድ ከቆመው ፈራጅ፣

ይኸነው ሐሳቡ የአምላክ ፍላጎቱ

ነፍስን እንድናድን ቀድሞ ከመሞቱ፣

ሆ! ዕድል ነው መታደግ ነፍስን ያህል ነገር

አምላክን አክብሮ አምላክን ማስከበር፣

ገንዘብ

የእናት ነፍስ አይገዛም ምንም ያህል ቢሹ

ካልተገኘ ዕድል ከአምላክ ከለጋሹ

* በጥቅምት 19 ቀን 2004 ዓ.ም. የሪፖርተር እትም ቴዲ አፍሮ ለነፍስ ዋጋ የከፈለውን አይቼ በጣም ደስ ብሎኛል:: ሰው በገንዘቡ ሊገዛው የማይችለውን ለመግዛት የመጀመርያ በመሆኑ ደስ ብሎኛል፤ ኮርቼበታለሁም:: እግዚአብሔር በጥበብና በማስተዋል በበለጠ እንዲገልጥልህ እለምናለሁ::

እድሜዋ በአንድ ድረ ገጽ በመጠቀሱ የ1 ሚሊዮን ዶላር ክስ ያቀረበችው ተዋናይትአንዲት ስሟ ያልተጠቀሰ ተዋናይት አማዞን ዶት ኮም የተባለ

ድረ ገጽ ዕድሜዋን በገጹ ላይ በማውጣቱ የ1 ሚሊዮን ዶላር ክስ እንዳቀረበችበት አሶሽዬትድ ፕሬስ ዘገበ::

ተዋናይቷ ክሱን የመሠረተችው የድረ ገጹ ድርጅት በሚገኝበት ሲያትል በሚገኘው የፌዴራል ፍርድ ቤት ሲሆን፣ ድርጅቱን ዕድሜዋን ከድረ ገጹ ላይ እንዲያነሣላት ብትጠይቀውም ፈቃደኛ ሳይሆን እንደቀረ ተዋናይቷ በክሱ ላይ አስረድታለች::

ተዋናይቷ በክሷ ላይ እንደገለጸችው የዕድሜዋ በድረ ገጹ ላይ መጠቀስ የትወና እድሎቿን ያሳጣታል:: ለዚህም እንደ ምክንያትነት የጠቀሰችው እንደሷ ላሉ ወደ 40 ዓመት ለሚጠጉ ሴት ተዋናዮች የሚፈልጉትን ሥራ ለማግኘት በጣም አስቸጋሪ ነው የሚል ነው:: ምንም እንኳን ችሎታውና ብቃቱ ቢኖራትም የዕድሜዋ መታወቅ በዳይሬክተሮች፣ በፕሮዲውሰሮችና በሙያው በሚገኙ ወሳኝ ሰዎች ዘንድ እንዳትፈለግ እንደሚያደርጋት በክሷ ላይ መግለጿን አሶሽዬትድ ፕሬስ ዘግቧል::

* * * * * * * * *

ጠጥቶ መርከብ በማሽከርከር የታሰረው ካፒቴን

የአንድ የዕቃ አቅራቢ መርከብ ካፒቴን የሆነ ግለሰብ ጠጥቶ መርከቧን በማሽከርከር ተጠርጥሮ መታሰሩን ሮይተርስ ዘገበ::

የ57 ዓመቱ ካፒቴን በቁጥጥር ስር በዋለ ጊዜ በተደረገለት የአልኮል ምርመራ በደሙ ውስጥ የተገኘው የአልኮል መጠን ጠጥቶ ማሽከርከር ከሚፈቀደው የአልኮል መጠን እጅጉ ያለፈ እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል::

እንደዚህ አይነት ጉዳይ ለመጀመርያ ጊዜ እንደገጠመው የገለጸው ፖሊስ ምንም እንኳ መኪና ባይሆንም ግለሰቡን ጠጥቶ በማሽከርከር ወንጀል ሊከሰው እንደተዘጋጀ ጠቁሟል::

ግለሰቡ ሊታሰር የቻለው ከባሕር ወጥቶ መሬት ላይ ከቆመ በኋላ እንደሆነ፣ በዚህ ጊዜ ምንም ዓይነት ነዳጅ እንዳልፈሰሰና ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳልደረሰ ሮይተርስ ዘግቧል::

ካሎሪክ ማለት ሙቀትን የሚሰጥ በሚሠራው ሥራ ብቻ በመገለጡ የታወቀ ሥነ ፍጥረቱ ግን ተመርምሮ ያልታወቀ በጣም ረቂቅ የሆነ (ፍሎዊድ) ነው:: ባጭሩ ካሎሪክ ማለት ሙቀት ማለት ነው:: ለምሳሌ ውኃ ከእሳት ላይ ሲጣድ እንዲሞቅና እንዲፈላ የሚያደርገው ካሎሪክ ነው:: እንዲሁም ደግሞ ካሎሪክ ማንኛውም አካል ጎን እንዲጨምር የማድረግ ጠባይ አለው:: ለምሳሌ ብረት በጋለ ጊዜ ይረዝማል ይህን የሚያደርግ ካሎሪክ ነው::

በውኃ ውስጥ ካሎሪክ ይገኛል:: ካሎሪክ ከሌለበት ግን ውኃ በረዶ ሆኖ ይጋገራል:: የካሎሪኩ መጠን ያነሰ ሲሆን ውኃው ይቀዘቅዛል ሲበዛ ግን ውኃው ወደ እንፋሎት እስኪለወጥ ድረስ

እየሞቀና እየፈላ ይሄዳል::ካሎሪክ በየአንዳንዶቹ አካላት ላይ ልዩ ልዩ ሥራ ይሠራል::

ለምሳሌ አሸዋን መስታዎት ያደርገዋል አፈርን ሸክላ ያደርገዋል::ከዚህ ሌላ ደግሞ ለምሳሌ አንዱን የጋለ ብረት በአንደኛው

ቀዝቃዛ ብረት ላይ ቢያስቀምጡት የሁለቱ ብረቶች ግለት እኩል እስኪሆን ድረስ በጋለው ብረት ውስጥ የሚገኘው ካሎሪክ ወደ ቀዝቃዛው ብረት ይተላለፋል:: ይህም አንድ ልዩ ጠባይ ነው::

ነገር ግን አካሎች ሁሉ ሙቀትን እኩል ስለማይቀበሉ ይህ ጠባይ በሁሉም ላይ ትክክል ሊፈጸምባቸው አይችልም:: ለምሳሌ ብረትን

እሳት ውስጥ ቢጨምሩት ይግላል እንጨትን ግን ሲጨምሩት ይነዳል እንጂ አይግልም:: ስለዚህ ሙቀትን የሚቀበሉና የማይቀበሉ አካሎች አሉ::

እንደዚሁ ሁሉ እብነ በረድን በእጅ ቢነኩት ይቀዘቅዛል:: ጨርቅን ግን ቢነኩት አይቀዘቅዝም:: በሁለቱ ውስጥ ያለው የቅዝቃዜ መጠን ግን ሲመዘን እኩል ነው:: እብነ በረድ መቀዝቀዙ በእጃችን ስንነካው በኛ ውስጥ የሚገኘውን ካሎሪክ ስለሚወስድ፣ ስለሚቀበል ነው:: ጨርቅ ግን ካሎሪክ አይቀበልም::

(ከበደ ሚካኤል፤ የዕውቀት ብልጭታ፣ 1999)

ዛሬ በታሪክየምኒልክ ሐውልት የተገለጠበት ቀን

በአዲስ አበባ ከተማ ያለውን የዳግማዊ ምኒልክን ሐውልት ያሠሩት ልጃቸው ንግሥት ዘውዲቱ ናቸው:: ሐውልቱ የተሠራው ጀርመን ነው:: የተሠራውም ከነሐስ ሲሆን የሠራውም ሐርቲል የተባለ ጀርመናዊ ነው::

ሐውልቱ ተመርቆ ለሕዝብ የተገለጠው ጥቅምት 22 ቀን 1923 ዓ.ም ነው:: ንግሥት ዘውዲቱ በዘመናቸው የአባታቸውን ሐውልት ቢያሠሩም ለምርቃቱ ሳይደርሱ በሞት ተቀደሙ:: ይህ ሐውልት ተመርቆ የተከፈተው በአልጋወራሽ ተፈሪ መኰንን የንግሥ በዓል ዋዜማ ዕለት ነው::

ኢብሊን ዋህ በአመራረቁ ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝቶ ስለነበር የአመራረቁን ሁኔታ ሬሞት ፒፕል በሚለው መጽሐፉ ውስጥ ገልጦታል::

‹‹… ጧት ሙዚቀኞች በአደባባዩ እየዞሩ ይጫወታሉ:: … የምኒልክ ሐውልት የሚመረቅበት ቀን ነው:: ሥነ ሥርዓቱ የሚጀመረው በ10 (በኛ 4) ሰዓት እንደሆነ ተነግሮናል:: ሥነ ሥርዓቱ ከሚጀመርበት ሰዓት ቀደም ብለን አይረን ራቬንስዳል እና እኔ ከበዓሉ ቦታ ሔድን:: የሰው መስቀያ የነበረው ዋርካ ዛፍ ከነበረበት ቦታ የምኒልክ ሐውልት ቆሟል:: ሐውልቱ በክፍት አረንጓዴ ሐር ተሸፍንዋል:: ዙሪያውንም ትንሽ አትክልት ቦታ አለች::…

‹‹ጥቂት ሰዎች መጡና ከመግቢያው ጀምረው ምንጣፍ አነጠፉ:: ትልቅና መልኩ ቢጫ የሆነ የጠረጴዛ ዣንጥላ ዘረጉና የሆቴል ደጃፍ አስመሰሉት:: ግማሹ በአካባቢው ያለውን ቅጠላ ቅጠል ይጠርጋል:: ባንድ በኩል የእጅ መደገፊያ ያለው ወንበር ተደረገ:: በሌላ ወገን ፎቶግራፍና ሲኒማ አንሺዎች ቦታ ለመያዝ ይጋፋሉ:: በሌላ በኩል ደግሞ ምንጣፉ ዘንድ ለመጠጋት የሚጋፋውን ሕዝብ ፖሊሶች ዱላ ይዘው ይከላከላሉ::

‹‹አራትና አምስት የሚሆኑ ኤሮፓውያን ተፈቅዶላቸው ምንጣፉ አጠገብ ቆመዋል:: እኛም ከነሱ ጋር ቆምን:: በየአስሩ ደቂቃ ፖሊስ እየመጣ ዞር በሉ፤ እልፍ በሉ ይለናል:: የፈቃድ ወረቀታችንን ስናሳይም ሰላምታ ሰጥተውን ይሄዳሉ::

‹‹ግማሽ ማይል በሚሆነው መንገድ የክብር ዘበኛ ሰልፈኛ ቆምዋል:: ቤልጂጋዊው ኮሎኔል ፈረስ ላይ ተቀምጦ ሰልፉን ያስተካክላል::

‹‹ዴሌጌሽኖች በዣንጥላ ስር በተደረገላቸው ወንበር ተቀመጡ:: ብዙ ጭብጨባ ሲጨበጨብ የአልጋወራሹ መምጣት ታወቀ:: አንድ ጥቁር ሰውየ በራሱ ላይ ወንበር ተሸክሞ መጣና በሌሎች ወንበሮች መሀል አስቀመጠው:: ወዲያው ዩኒፎርም የለበሱ ሰዎች መጥተው መቀመጫውን ያስተካክሉ ጀመር:: ጦር የያዙ ወታደሮች ከአለፉ በኋላ አንዲት አውቶሞቢል ደረሰች:: እንደቆመችም በሐር ዣንጥላ ተሸፈነች:: አልጋ ወራሹም ከወንበራቸው ላይ ሔደው ተቀመጡ::

‹‹ጥቂት ቆይቶ ሻለቃ ሲንክለር ሙዚቀኞቹን ይዞ መጣና በመሀል አደባባይ ቆመው ሙዚቃ ያሰሙ ጀመር:: ከዚህ በኋላ በፕሮግራሙ መሠረት ሁሉ ነገር ይካሄድ ጀመር:: አልጋ ወራሹ ንግግር ካደረጉ በኋላ ገመዱን ስበው ሐውልቱ የተሸፈነበትን አረንጓዴውን ሐር ሲገልጡ ሐውልቱ ያብረቀርቅ ጀመር::

‹‹ግሪካዊው ኮንትራክተርም መሰላል አቅርቦ ሐውልቱ ላይ ወጣን:: ሐውልቱ የተሸፈነበትን ጨርቅ በሙሉ አነሳው:: ሙዚቀኞች እየተጫወቱ ሐውልቱ ከተመረቀ በኋላ ሁላችንም ሄድን::…›› ብሏል::

(ጳውሎስ ኞኞ፤ አጤ ምኒልክ፣ 1984)

ነገ - በታሪክጥቅምት 23 ቀን 1923 ዓ.ም. ልዑል አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኰንን ‹‹ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ

ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ›› ተብለው በኢትዮጵያ ነገሡ::

ጥቅምት 22 ቀን 1923 ዓ.ም. ለሕዝብ የተገለጠው የዳግማዊ ምኒልክ ሐውልት

ካሎሪክ

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/መስፍ

ን ሰሎ

ሞን

Page 20: Reporter Issue 1201

ገጽ 20|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

የጨረታ ማስታወቂያበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የመንበር ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በተሠየመ ኮሚቴ የተለያየ መጠንና አገልግሎት ያላቸው 10 ያገለገሉ መኪኖችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም

1. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መዝጊያ ቀንና ሰዓት ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት አምስት ኪሎ ከሚገኘው ጠ/ቤተ ክህነት 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 7 በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡

2. ተጫራቾች የጨረታ መወዳደሪያ ሰነዳቸውን በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ እስከ ህዳር 25 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተገለጸው ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ማስገባት አለባቸው፡፡

3. ተጫራቾች ለሚገዙት ተሽከርካሪ ከአቀረቡት ዋጋ 20% ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ /CPO/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

4. በአንድ የጨረታ ሰነድ ከአንድ መኪና በላይ መጫረት አይቻልም፤5. ተጫራቾች በጨረታው አሸናፊ የሆኑበትን ተሽከርካሪ አጠቃላይ ዋጋውን

ከፍለው በ15 ቀን ውስጥ ተረክበው ማንሣት አለባቸው፡፡ 6. ለጨረታ ማስከበሪያ የተያዘው ገንዘብ አሸናፊ ለሆኑት ከሚገዙት ተሽከርካሪ

ዋጋ ክፍያ ጋር ታሳቢ ይሆናል፤ ተሸናፊ ለሆኑት ግን ያስያዙት ገንዘብ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡

7. ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን አንሥቶ እስከ 1 ወር ይቆያል፤ 8. ጨረታው ህዳር 25 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት በጠቅላይ ቤተ ክህነት

አስተዳደር ጉባኤ አዳራሽ ይከፈታል፤ 9. የስም ማዛወሪያ ወጪዎችና የመንግሥት ግብርን ገዢ ይችላል፤ 10. በመኪናዎች ላይ የሚከፈል ዕዳ ቢኖር ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ይከፍላል፤ 11. ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ

የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በሞባይል ስልክ 09 20 19 08 36 0910 99 19 99 0911 37 61 21

ዘወትር በሥራ ቀን ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡

INVITATION TO TENDERTo all Contractors of category GC/BC Class I with license renewed for the

year1. SCFCU/Sidama coffee farmers cooperative union/ now invites wax sealed bids from eligible

bidders for furnishing the necessary material, labour and equipment for the construction and

completion of Modern G+9 mixed use building at Hawassa.

2. The bidder have to present original registration certificate from the Federal Ministry of

Finance & Economic development, renewed license for the year; Trade License, Construction

license, Clearance letter and VAT registration certificate, TIN certificate to obtain the bidding

document.

3. Eligible bidders are required to submit Technical and Financial proposals. A contractor

will be selected under Quality-and cost-based selection procedures described in the bidding

document.

4. A complete set of document may be purchased by any interested eligible bidder at Sidama

Coffee Farmers cooperative Union.

Address: Nefas Silk Lafto Sub City

Street: Debre Zeit Road, In front of Nifas Silk Paint Factory

Floor/Room Number: Dawi Building second floor

Town/City: Addis Ababa

POBox No/Postal Code: 122062

Telephone: +251-11 440 7165/251 114403919

Facsimile number: Fax +251-11-440-7166

Against non refundable fee of ETB Birr 2000.00 (two thousand)

5. All bids must be accompanied by a bid security, in the form of certified cheque or a Bank

Guarantee of amount ETB Birr 100,000.00. Bids must be delivered to Sidama Coffe Farmers

Cooperative Union before Monday Hedar 18/2004 E.C at 8:00 local time, at which time

the Technical proposal will be opened in the presence of the bidders who wish to attend. Bids

shall be valid for a period of 60 days after bid opening.

6. The Financial proposal of the bidders who pass the qualification criteria shall be opened, in

the presence of the bidders who wish to attend, on the date to be announced by the employer.

7. SCFCU/Sidama coffee farmers cooperative union reserves the right to accept or reject any

or all bids.

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 0100/2011

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በመቀሌ ከተማ እያከናወነ ላለው የአፓርትመንት ግንባታ የሦስተኛ እጅ ልስን ሥራ በጅብሰም ከዚህ በታች በተዘረዘረው መልኩ ማሠራት ይፈልጋል፡፡

No Description Unit Quantity Unit Price

Total Price

1 Supply and apply 3rd coat Gypsum plaster on two coat plastered wall beam & column including edge & fuca works done vertically & horizontally.

M2 100,000

2 Supply & apply 3rd coat Gypsum plaster on two coat plastered ceiling, belly & side of sair case including edge & fuca works done vertically & horizontally.

M2 28,000

ስለሆነም፡-1. ተጫራቾች ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን

አለባቸው፡፡2. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚያቀርቡት ገንዘብ በተጫራቾች መመሪያ ተራ ቁጥር 7.3 መሠረት በባንክ በተረጋገረጠ C.P.O መሆን አለበት፡፡3. ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን የማይመለስ ብር 100.00/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋናው

መ/ቤት የግዥ የሥራ ሂደት ኬዝ ቲም ቢሮ ቁጥር 14 በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡4. ተጫራቾች ለሥራው የሚያስፈልገውን ሙሉ መገልገያ መሣሪያዎች በራሳቸው ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡5. ለጀብሰም ማዋሀጃ የሚውለውን ውኃ በራሱ ማቅረብ የሚችል መሆን አለባቸው፡፡6. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ ህዳር 21 ቀን 2004 ዓ.ም. ከጥዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ

ማስገባት ይኖባቸዋል፡፡7. ጨረታው ህዳር 21/2004 ከጥዋቱ 4፡15 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡8. ድርጅቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ፡- የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝየቀጥታ ስልክ 0114-40-34-34/33

የማዞሪያ ስልክ 0114-42-22-70/71/72ፖ.ሳ.ቁ 3414

ፋክስ ቁ.0114-42-07-46/0114-40-04-71ወሎ ሰፈር የቀድሞው ኖሬላ ግቢ

Page 21: Reporter Issue 1201

|ገጽ 21 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

− ክቡር ሚኒስትር በጭራሽ ሊያስቡና ሊሰጉ አይገባም:: እኛ አለን አይደለም ወይ?

− አይ ምናልባት አንዳንድ ለበጎ የሠራሁት ነገር ሌላው ከሰማው በተሳሳተ መንገድ ሊተረጉመው ይችላል:: ለስም ማጥፋት ይመቻቸው ይሆናል ብዬ ነው::

− እንዴ ክቡር ሚኒስትር አንደኛ ሚስጥሩን ሊያውቁት አይችሉም:: ካወቁትም ለልማት ተብሎ የተደረገ ነገር ነው እንላለን:: እኛ በእርስዎ ምክንያት መሬት፣ የባንክ ብድር፣ ከቀረጥ ነፃ ፈቃድ፣ ግብር ያለመክፈል ከለላም አግኝተናል:: ነገር ግን ብቻችን አልለማንም:: ለስንቱ ደሃ የሥራ ዕድል ፈጥረናል:: ልማት ማለት ይህ አይደለም ወይ?

− (ሌላው) እስቲ አንድ ሰው ደፍሮ በእርስዎ ላይ ጥያቄ ያንሳ፣ የእጁን ያገኛል:: መከላከል ብቻ ሳይሆን ማጥቃትም እንችላለን:: ከአሁን በፊት የሞከሩት ምን እንዳገኙ የሚረሳ አይመስለኝም:: ክቡር ሚኒስትር እርስዎ ብቻ እኮ አይደሉም የእኛ አለኝታ፤ እኛምኮ የእርስዎ አለኝታ ነን::

− አውቃለሁ፣ አውቃለሁ፤ እየጠጣችሁ እንዴ ምነው ምነው? እኔ ጉዳዩን ያነሳሁት ምናልባት ያልታሰበ ነገር ከመጣ አስበንበትና ተጠንቅቀንበት እንድንቆይ ብዬ ነው:: በመንግሥት ዙሪያ አሁን ወስነን ማጥራት፣ መገምገም፣ መጠናከር፣ ማባረር የሚሉ ቃላትና እንቅስቃሴዎች እየበዙ ስለመጡ ነው::

− እንዴ ክቡር ሚኒስትር የፈለጋቸውን ይገምግሙ፣ ያጥሩ ሌላው በእኛ ላይ ከያዘው መረጃ፣ እኛ በሌላው ላይ የያዝነው መረጃ አይበዛም ወይ?

− እሱስ ትክክል ነህ፣ ማን ይቀድማል የሚል ጥያቄ ይነሳል እንጂ::

− ክቡር ሚኒስትር ለዚህምኮ መልሱ ቀላል ነው::

− ለምን እኛ አንቀድማቸውም? እንቅደማቸው::

− እንዴት ነው የምንቀድማቸው?

− ቀላል ነው ክቡር ሚኒስትር:: አስቀድመን እኛን ሊያጠቁ የሚፈልጉትን ስም ዝርዝር እንለይ:: በየአንዳንዱ ላይ አንዳንድ ነገር እያዘጋጀን በአለን ኔትዎርክ በኩል በከተማው እንዲወራና እንዲጋነን ማድረግ ነው:: ያኔ እንኳን እኛን ሊያጠቁ፣ ይሸማቀቃሉ:: የእኛን እርዳታ ይፈልጋሉ::

− ምናልባት አንዳንዶቹ ሊፈሩና ሊሸማቀቁ ይችላሉ:: አንዳንዶቹ ግን ላይሸማቀቁና እንደውም ይበልጥ ሊዳፈሩ ይችላሉ::

− ለእነሱ ደግሞ ሌላ መንገድ እንፈልጋለን ክቡር ሚኒስትር:: እንዴ ብዙ ልምድ አለን እኮ::

− ብቻ እንዘጋጅ፣ አንዳንዱ ንፁህ ነኝ ብሎ ይተማመናል::

− (ሌላው) ክቡር ሚኒስትር ልምዳችን እኮ ቆሻሻን ማጠብ ብቻ አይደለም:: ንፁህን ማቆሸሽም ልምዱ አለን፣ እንችልበታለን::

− (ሌላው) በሁሉም መንገድ እንዘጋጅ:: ዝግጅታችን ግን እዚህ ብቻ ሳይሆን ውጭም ይሁን::

− ትክክል ሁሉም ጋ እንዘጋጅ:: ዶክሜንታችንን እንዳይሰርቁ እንጠብቅ:: ጠላታችንን እንከታተል! እንወቅ! እንቅደም! በሉ እየጠጣችሁ እስካሁን ሁለት ጠርሙስ ውስኪ ብቻ፣ ምነው ምነው?

(ጨዋታው ተሟሙቆ ክቡር ሚኒስትር እስከ ግማሽ ሌሊት ሳይተኙ ቆዩ:: ቢሮ የገቡትም አርፍደው ነበር:: ምነው አረፈዱ ለማለትም ጸሐፊዋ ቢሯቸው ገባች)

− ችግር አለ? ክቡር ሚኒስትር፣ አለወትርዎ አረፈዱ ብዬ ነው:: ፊትዎም ድክምክም ብሏል?

− አንዲት አሮጊት ዘመድ ታማ እሷን ለማሳከም ከሆስፒታል ወደ ሆስፒታል ስንዞር

እንቅልፍም በዓይኔ ዞር አላለም::

− ታዲያ ቤት ሄደው ለምን ትንሽ አረፍ አይሉም?

− የአገርና የሕዝብ አደራ ተሸክሞ እረፍትና እንቅልፍ ይኖራል ብለሽ ነው?

− ደስ ይላል::

− ምን ደስ ይላል?

− ሌላው ለመስረቅ፣ ለመዝረፍ፣ ስም ለማጥፋት እንቅልፍ አጥቷል:: እርስዎ ግን አገርና ሕዝብ ለማገልገል እረፍት አጥተዋል::

− ብቻዬን አይደለሁም፣ እዚህ ቢሮም እንደአንቺ የመሰሉ የሚያስቡ ሠራተኞች አሉ::

− አሉ አዎን ግን በተፃራሪው ደግሞ ለአገር የሚሠራውን የሚያደናቅፉ አሉ::

− እኛ መሥሪያ ቤት ውስጥ አሉ ብለሽ ነው?

− እንዴ አሉ:: አሁን በመሥሪያ ቤታችን ተስፋፍቶ ያለው ወሬ ግዥና ሽያጭ በሙስና የተጨማለቀ እንደሆነ፣ እርስዎ የመሥሪያ ቤትዎን ሥራ ትተው ለሌሎች መሬት እየሰጡና የባንክ ብድር እያስፈቀዱ እንደሚውሉ፣ ውጭ አገር ገንዘብ እንዳለዎት ነው:: ይህ ሁሉ ዶክሜንት እንደተገኘለትና በቅርቡ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤትና ለፀረ ሙስና ኮሚሽን እንደሚላክ፣ ኧረ ስንቱ?

− ምን? እንደዚህ እየተወራና እየተደረገ ነው?

− አዎን፣ እንደውም አንድ ባለሥልጣን በ83 ሚሊዮን ብር ተከሰዋል የሚል ወሬ በመገናኛ ብዙኃን ሲሰራጭ፣ የእኛ ሚኒስትር 347 ሚሊዮን ብር ሰርቀው የለም ወይ እየተባለ በግቢው ይወራል:: የጠላት ወሬ::

− አሁን በዚሁ መሥሪያ ቤትም፣ በድሮ መሥሪያ ቤቴም በሠራሁት ሥራ መንግሥት ያመሰግነኛል::

− እኔኮ አውቃለሁ ክቡር ሚኒስትር:: ምን እንደሚወራ እንዲያውቁ ብዬ ነው እንጂ:: እንደውም ምን እየተባለ ነው መሰለዎት? ከድሮ መሥሪያ ቤትዎ መልቀቅ አይፈልጉም ነበር:: ሲለቁም ብዙ ነገር አበላሽተው ነው የወጡት እየተባለ ነው:: በድሮ መሥሪያ ቤትዎ እርስዎ ያበላሹትና የተከሉት መርዝ ለአሁኖቹ ኃላፊዎች ለማስተካከል አስቸጋሪ ሆኗል እየተባለ ነው::

− ጓደኞቼም ወዳጆቼም ስለእኔ ሃቀኝነት ይመሰክራሉ::

− እንደውም ረስቸው ነበር:: ከጓደኞቻቸውና ከወዳጆቻቸው የተውጣጣ አደገኛ የማፍያ ቡድን አልዎት እየተባለም ይወራል::

− ማ እኔ?

− አዎን! ወሬ ነው እንጂ::

− እንደዚህ የሚያወሩት እነማን እንደሆኑ ታውቂያለሽ? ስማቸውን? ክፍላቸውን?

− አዎን አውቃቸዋለሁ:: የልብ ልብ ማን እንደሰጣቸው እንጃ እንጂ አሁንኮ በግልጽ ነው የሚናገሩት፣ እንደውም ይህንን ሙስና ለማጋለጥ እንዲያመቸን ሥራ እንለቃለን እያሉ ናቸው::

− ይኸውልሽ አንቺ ጥሩ ሰው ነሽ:: ለአገርና ለወገን ታስቢያለሽ:: ተከታተያቸው:: የራስሽን ሰዎች አሰባስቢና ተቃወሚያቸው:: ለዚህ ሁሉ ሥራ ገንዘብ ያስፈልግሻል ለጊዜው ሁለት መቶ ሺሕ ብር እሰጥሻለሁ::

− እ…

− አዎን ሁለት መቶ ሺሕ ብር::

− ገንዘቡን አይደለም ክቡር ሚኒስትር፣ ሥራዬ ከሆነ ክፍያ አያስፈልግም ማለቴ ነው::

− ይህንች ዳር አድርሺና ሲሳካ መኪናም ይገዛልሻል::

− የእኔ ስልክም እየጠራ ነው ክቡር

ሚኒስትር አንዴ አንስቼው ልምጣ::

(ጸሐፊዋ ደንግጣ ወጣች:: እሳቸውም ደንግጠዋል:: ሞባይላቸው ጮኸ)

− ጎሽ እንኳን ደወልክ አሁን ቶሎ ና::

− ብቻዬን ልምጣ?

− ወዳጅህን ይዘህ ና፣ በር ላይ ስትደርስ እንዳይፈትሹህ ሾፌሩን በር ላይ እንዲቆይ አደርጋለሁ::

− እሺ ክቡር ሚኒስትር መጣሁ::

(ጸሐፊዋ ክቡር ሚኒስትሩ ቢሮ ገባች)

− እርስዎን በአስቸኳይ እፈልጋለሁ የሚል ሰው ቢሮዬ ገብቷል ክቡር ሚኒስትር::

− አንዴ አንቺ ቢሮ ጋር ይቆይ:: ቡና ጋብዢው አውሪው ሌላ ሰው እንዳይኖር አድርጊ ብቻችሁን ሁኑ::

(ወደ ቢሮዋ ተለመለሰች)

− አቤት ምን ልታዘዝ?

− ማኪያቶ አትጋብዢኝም እንዴ?

− እሺ አንዴ ልዘዝ (በስልክ አዘዘች)

− ክቡር ሚኒስትሩ ስለአንቺ ብዙ ነገር ያወራሉ::

− ምን ይላሉ?

− በሕይወቴ ውስጥ የምመኘው እሷን መርዳት ነው ሲሉ እሰማቸው ነበር::

− እና?

− እና እኔም በአቅሜ ልርዳ ብዬ ነው የመጣሁት:: ይኼ ሁለት መቶ ሺሕ ብር ነው:: ሌላ ጊዜም መኪና እገዛልሻለሁ ወይም በተመቸሽ ሰዓት እንገናኝንና ሄደሽ መኪናውን ትመርጪያለሽ::

− ኋላ መኪናውን ስንመርጥ ገንዘቡን ያኔ ትሰጠኛለህ:: አሁን ሰው እንዳይመጣ ቦርሳህ ውስጥ ክተተው:: ቶሎ በል::

− ከሰዓት እንገናኝ?

− እሺ::

− ይኸው የሞባይል ቁጥሬ::

− እሺ::

(ጸሐፊዋ አሞኛል ብላ ከሰዓት በኋላ ቢሮ አልገባችም:: ክቡር ሚኒስትሩ በገንዘቡ ተደስታና ለመኪናው ግዥ ቸኩላ ነው ብለው በመቅረቷ ቅር አላላቸውም:: በሞባይላቸው ሲደወል ቁጥሩን ሳያዩ ማነጋገር ጀመሩ)

− ይቅርታ ክቡር ሚኒስትር የደወልነው ከሌላ ቢሮ ነው::

− ምን ቢሮ?

− ከፀረ ሙስና የምርመራ ክፍል::

− ለምን?

− ለምርመራ እንፈልግዎታለን::

− ምን የሚሉት ምርመራ?

− ከመሥሪያ ቤትዎ ሠራተኞች የደረሰን ክስና ጥቆማ አለ::

− ምን የሚል?

− 347 ሚሊዮን ብር ሰርቀዋል የሚል::

− እ…

− እ… የበላይ አካል ማወቅ ያለበት ይመስለኛል::

− የእርስዎ ጉዳይ ለበላይም ተልኳል:: ይታወቃል:: እንደሚመረመሩም ታውቋል::

− እሺ አሁን መጣሁ::

(ሾፌራቸው ጋ ደወሉና በአስቸኳይ ቤንዚን እንዲሞላ አዘዙ:: እሱም ሞልቶ መጣ ገቡ)

− አስቸኳይ ስብሰባ ሞያሌ ስላለ ወደዛ እንሂድ::

− ሞያሌ?

− አዎን::

− ልብስ አንይዝም ታዲያ?

− መንገድ ላይ እንገዛለን:: እዛ በድርቅ የሚታዩ ወገኖች ስላሉ በአስቸኳይ አይተህ ሪፖርት አቅርብልኝ ስለተባልኩ ነው:: ኮሚቴ ተቋቁሞ የዛ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነኝ::

− እሺ አንዴ ባለቤቴ ጋር ልደውል::

− ደውል እኔም ባለቤቴ ጋ እደውላለሁ::

(ክቡር ሚኒስትሩ ሊወጡ ሲሉ የፖሊስ መኪና መጥቶ በር ላይ ቆመ፣ ፖሊሶች ወርደው ሚኒስትሩን ይዘው ሄዱ:: ምርመራ ተካሄደ:: ክስ ተመሠረተባቸው:: እሳቸውም ጠበቃ ቀጠሩ:: ከጠበቃቸው ጋር እየተወያዩ ናቸው)

− ችግር የሚኖር ይመስልሃል?

− አዎን አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እየገባን ነው::

− ምን የሚያስቸግር ነገር አለ?

− ዶክሜንቱ የቀረበው በእርስዎ መሥሪያ ቤት ሠራተኞች ነው:: ሠራተኞቹ በእርስዎ ላይ ተነስተዋል:: − እሱ አያሳስብህ እኔን የሚደግፉ ሃቀኛ

ሠራተኞች አሉ:: − ጥሩ ካሉ ስማቸውን ይንገሩኝና እኛም

ለምስክርነት እናቅርባቸው:: − እሺ:: − እሺ ይንገሩኝ ክቡር ሚኒስትር:: − ወይ ክቡር ሚኒስትር… በል ብቻ ስም

ያዝ፣ አንዱ የእኔ ሾፌር፣ ሁለተኛ የእኔ ጸሐፊ:: − አንዴ አንዴ ክቡር ሚኒስትር:: − ምነው?

− እነሱንማ ከሳሽ በምስክርነት መዝግቧቸዋል:: ይኸው በክሱ ዝርዝር ውስጥ በምስክርነት ገብተዋል::

− የእኔ ሾፌርና የእኔ ጸሐፊ በእኔ ላይ ሊመሰክሩ፣ ውሸት ነው:: ውሸት ነው:: ስማቸው ቢመዘገቡም እኔን ደግፈው እንደሚመሰክሩ አትጠራጠር፣ እንትን አድርግ::

− ምን?

− ስልክ ቁጥር ልስጥህና ጓደኞቼንና ወዳጆቼን አግኛቸው::

− የእርስዎ ሁለት ጓደኞች ዛሬ ጧት ደውለው ነበር::

− ምን ብለው?

− አንዱ ጸሐፊዋ በእሳቸው ላይ ልትመሰክር ተዘጋጅታለች ተጠንቀቁ ብሎ::

− ምን ብላ ልትመሰክር ነው አለህ?

− ሁለት መቶ ሺሕ ብር በጥሬ ገንዘብ እንዲሁም አዲስ መኪና ጉቦ ገዝተው አፌን ሊዘጉና ሙስናን ሊደብቁ ሞክረዋል ብላ::

− ምን? በእኔ ላይ ልትመሰክር?

− እንደውም ምስክር ብቻ ሳይሆን ከሳሽም ነኝ እያለች ነው:: ስሟም ከሌሎች ሠራተኞች እንዲካተት አድርጋለች::

− ጉድ!

− ክቡር ሚኒስትር ሌላው ወዳጅዎ ደግሞ ሾፌሩም ሊመሰክር ነው ተጠንቀቁ ብሏል:: ሚስቴ ጋ እደውላለሁ ብሎ የደወለው ፖሊሶች ጋር ነው ብሎኛል:: በዚህም ምክንያት ነው ፖሊሶች ግቢ ድረስ የመጡት::

− እሱም በእኔ ላይ ሊመሰክር?

− አዎን ክቡር ሚኒስትር::

− ምን ብሎ?

− ‹‹በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ ሊጠፉ አቅደው ነበር›› ብሎ::

(ክቡር ሚኒስትሩ አንዳንድ ያሳሰቡዋቸው ጉዳዮች ስላሉ ከመሥሪያ ቤታቸው፣ ከሌላ መሥሪያ ቤት፣ ከግል ዘርፉም የሚያምንዋቸውን ሰዎች በቤታቸው እራት ጋብዘዋል:: እያወሩም ናቸው)

Page 22: Reporter Issue 1201

ገጽ 22|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

EXPRESSION OF INTEREST (EOI) FOR CONSULTANCY SERVICES TO CONDUCT

A RAPID ASSESSMENT OF HIV SITUATION IN PRISON SETTINGS IN ETHIOPIA

REF NO: TA/ET/020/11

The United Nations Office on Drugs and Crime (UNODC) is mandated to assist Member States in their struggle against illicit drugs, crime and terrorism; in Ethiopia UNODC is, inter alia, working with the Government to carry out a rapid assessment on HIV and TB amongst the prison population.

The Technical Support Facility for Eastern Africa (TSF-EA) is a UNAIDS supported mechanisms which provides high-quality technical assistance to countries on strategic planning, implementation, monitoring and evaluation of national HIV programmes.

On behalf of UNODC, TSF-EA will support the Government of Ethiopia’s Federal Prison Administration to carry out the proposed rapid assessment of the HIV situation in prison settings; and now invites eligible local groups of individual consultants, consulting firms/organizations or consortia to submit an expression of interest for consideration to provide the service. The specific objectives of the rapid assessment of the HIV situation in prison settings in Ethiopia are to:1. Gather evidence-based qualitative and quantitative data on HIV prevalence and risk

behavior in the prison settings in Ethiopia;2. Analyze existing legislative and policy framework/response for identification of

potential policy barriers; 3. Analyze current programmatic responses in terms of the availability, nature and

effectiveness of the existing HIV services and gaps therein for comprehensive HIV prevention, care and treatment in the prison settings in Ethiopia;

4. Make recommendations for a comprehensive strategy/action plan on HIV prevention, care and treatment in the prison settings;

5. Participate in the validation workshop and incorporate all necessary comments in the final rapid assessment;

6. Provide weekly/monthly or any fixed date written periodic updates on progress of the rapid assessment;

7. Ensure all data collection tools are translated into local languages, back translated into English to ensure accuracy.

Interested parties must provide information which demonstrates their capacity, relevant experience together with a broad outline of their proposed approach to the assignment. They should also outline the skills sets and mix of the proposed staff to successfully undertake the rapid assessment. The bidders should provide a list of previous similar assignments undertaken, and where relevant, should include their corporate profile.

The responding consulting organizations or groups of individual consultants or consortia are also expected to provide source documents/brochures and a good description of any similar assignments they have undertaken in related settings. The information/references provided in support of the submitted EOI should include the names and contacts of at least two clients served over the last five years. The consulting firms/organizations or groups of individual consultants or consortia which submit the most compelling expressions of interest (EOI) will be invited to develop a full proposal for consideration and award to carry out the rapid assessment as per the TORs. TSF EA is not, and shall not be, liable or responsible for any costs or expenses incurred by a proposing organization or consultant in the preparation, submission and production of a expression of Interest or for any work performed by the proposing firm prior to the execution of a final agreement. All such costs and expenses are the sole and absolute responsibility of the proposing firm or consultant. TSF EA reserves the right to decline any and all submissions. All submissions shall remain valid for a period of thirty (30) days from the stated deadline.

The EOI, NOT EXCEEDING 10 pages, should be submitted in BOTH soft and hard copy as follows:

In hard copy submitted and received not later than TIME 16 November 2011 to:Technical Support Facility-Eastern Africa (CAFS Ethiopia)Gerji Sami Bldg 2nd FlrP.O Box 33101Addis Ababa EthiopiaTel: +251 (0) 11 629 8405/116298399A soft copy of the EOI must be submitted by the respondent to the following e-mail addresses and received by the same deadline: [email protected] and copied to: [email protected].

አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅትየጨረታ ቁጥር አከአአድ/09/04

አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የተበላሸ የአውቶቡስ

ማጠቢያ ማሽን ባለሙያዎችን አወዳድሮ ማሳደስ ይፈልጋል፡፡

በዚሁ መሠረት

1. ማሽኑን ለማደስ የሚችል ድርጅት የብቃት መረጃውን በመያዝ

ለእድሳቱ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በዋና መስሪያ ቤት ቢሮ ቁጥር 209

የማይመለስ ብር 100 በመክፈል መውሰድ ይቻላል፡፡

2. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 2,000.00/ ሁለት

ሺህ ብር/ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ ቼክ በአንበሳ የከተማ

አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ስም ማስያዝ አለባቸው፡፡

3. ጨረታው ኅዳር 08 ቀን 2004 ዓ.ም. ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ

በተመሳሳይ ቀን ከጥዋቱ በ4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው

በተገኙበት ላይ ይከፈታል፡፡

4. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ

የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅትአዲስ አበባ

ስ.ቁጥር 011 629-41-86

Crystal Tannery S.CoBid for consultancy

Crystal Tannery S.Co is one of the finished Leather manufacturing industries in Ethiopia. Crystal Tannery S.Co would like invite all authorized consultants to implement ISO Quality management and Environmental management systems.

Bidders must have:-

Renewed professional license & business license Registered certificateTax Identification number (TIN) certificate

Bidders are expected to come to Bole, friendship building office # 408 and collect the TOR with non returnable fee birr 100. The bid document should be returned within 10 working days after this announcement. Bidders should submit the Eligibility document, technical proposal and financial proposal separately for more information contact.

01186017820114348899

Page 23: Reporter Issue 1201

|ገጽ 23 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

9 ACP RPR 139/7ACP – EC EnERgy FACility ACtion

lAy VoluntEERs intERnAtionAl AssoCiAtion (l.V.i.A.) has a Vacancy for:

PRoJECt CooRDinAtoR

Title of the action: Hydro-Bio-Power: livelihood improvement in rural area through collaborative development of renewable energy sources in Oromia and Southern Nations Regional States of Ethiopia

Location(s) of the action: Ethiopia: Oromia and SNNPR Regions, Woreda Shashemene, Halaba, Bensa, Kokosa, Nansebo.

1. Background

This project is funded by European Commission

LVIA is currently implementing an Energy Facility project titled “Hydro-Bio-Power: livelihood improvement in rural area through collaborative development of renewable energy sources in Oromia and Southern Nations Regional States of Ethiopia” and co-financed by European Commission.Currently the project has been amended and extended in order to close timely on all the expected activities (5 hydropower schemes and Bio-GAS implementations). The project has a serious delay on the expected plan of action and the figure required will take the lead on ensuring the proper prosecution of the activities and the successful closing of the project in the expected time (estimated for June 2012).The project coordinator will have the support of highly skilled technical consultancies firm on the engineering part of the project, while the main efforts have to be invested in the proper follow-up and boosting of the already ongoing activities.

2. Purpose of the Post:The officer will program planning, administration, implementation, monitoring and evaluation of the activities of the above mentioned project, data analysis and progress reporting both narrative and financial, in coordination of a team composed of expatriates and local staff.

3. Major duties and responsibilities: Organize and ensure the progress of all the project activities as per the work plan of action. Supervise and coordinate field staff on construction sites. Ensure the timely respect of work progress on hydropower schemes construction sites. Represent LVIA with local and regional authorities, and develop with them, the

EUexpertsandthepartnerNGOs,collaborativerelationshipsandeffectivecommunication.

Manage the project staff.

Approve payments at project level and manage the project bank account opened on behalf of LVIA.

Selectlow-levelstaffonsite,participatewithC.Rep.totheselectionofhigh-levelstaff according to the “worker guidelines” of LVIA Ethiopia and facilitate training and capacity building of staff.

Organize and supervise the timely delivery or payments and follow up with finance, administrative, supply and program staff on processing of payments, advances to partners and liquidation of accounts.

Support, coordinate and supervise the timely preparation of accountancy at project and area level, managing the cash flow and ensuring the financial follow-up on the project.

Manage and ensure the proper collaboration with the partners. Undertake field visits to project sites, work with beneficiary groups, organize and conduct

assessments as necessary. Communicate with counterpart local authorities and communities on project details. Prepare reports on project activities for EU, governments and project partners. Prepare background materials for use in discussions and briefing sessions. Undertake arrangements for visits to project sites for partners and authorities, which include

providing information and briefing on project activities and status. participate and actively contribute to the preparation of project proposals related with the

Energy Facility sector activities.The position is referring to:

LVIA Ethiopia Country Representative. LVIA HQ Project Desk Officer and LVIA HQ Administrative and Finance Officer for

specific assignments.Duty Station:

Ethiopia, Shashemene Town (LVIA office). Frequent trips to Addis Ababa can be required. Frequent and constant field supervision to working sites is strictly required.

4. Qualifications, Experience & SkillsMinimum requirements:

University Degree; Five continuative working years experience as Project Coordinator in African Countries on EU

funded project. Perfect knowledge of computer systems and MS Office package (especially Word and Excel); Good communication, analytical skills and proved experience on construction sites supervisions

(even for private sector); Knowledge of EU rules and regulations (Preparation of financial reporting, Tenders procedures); Fluency in English; Experienced in field work;

Added valuable requirements: Master Degree on engineering or similar. Previously working experience in Ethiopia; Proved experience on site supervision and work coordination (even for private sector) on

hydropower sites construction;5. Others

Duration of the contract: 01/12/2011 for 6 Months with possibility of renewable;

Contract conditions (as per LVIA salary scale): from 10,000 ETB up to 16.000 ETB net-salary monthly (according to the experience of the

candidates);

Insurance coverage;

6. How to applyInterested and qualified candidates should send their applications with updated CV.

Human Resources Manager L.V.I.A.

Corso IV Novembre, 2812100CuneoItaly

In Ethiopia (highly recommended):LVIA Ethiopia Country Representative

P.O. Box 102346Addis Abeba

EthiopiaOr email (by putting as email object EF PC Vacancy ETH):

TO: [email protected]

AND in Cc:[email protected]

[email protected][email protected]

EMAIL APPLICATIONS ARE HIGHLY APPRECIATEDPlease note that documents submitted along with your applications will not be returned.

Deadline for submission of proposals: 12th November 2011Only short-listed applicants will be contacted and selection session will be organized accordingly,

tentatively in the last 2 weeks of November 2011.

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

ተ.ቁ የሥራ መደብ የትምህርት ደረጃ የሥራ ልምድ 1 ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ቢኤስሲ.ዲግሪ ምህንድስና 6/ስድስት/ ዓመትና ከዚያ በላይ በመንገድ ሥራ

ላይ የሥራ ልምድ ያለው ሆኖ ቢያንስ 2ቱን ዓመት በሥራ አስኪያጅነት ያገለገሉ፡፡

ደመወዝ፣ በስምምነትብዛት፣ 3(ሦስት)የሥራ ቦታ በየፕሮጀክቱ

ከዚህ በላይ በተመለከተው የሥራ መደብ ለመወዳደር የምትፈልጉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ5/አምስት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የትምህርት ማስረጃ እና የሥራ ልምዳችሁን በመያዝ አስተዳደር ክፍል በመቅረብ መመዝገብ የምትቸሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

አድራሻ፡ ብስራተ ገብርኤል ቤተክርስትያን ጀርባ የድሮ አይሮፕላይን ማረፊያ አካባቢ ሳትኮን ዋናው መ/ቤት ስልክ ቁጥር 011 372 78 22 ወይም 011 372 71 74

Page 24: Reporter Issue 1201

ገጽ 24|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

Vacancy AnnouncementThe Ethiopian Rainwater Harvesting Association (ERHA) is a registered non-governmental and non- profit-motivated national organisation established to promote rainwater harvesting technologies to address shortage of water for domestic supply, food production and environmental needs; with a Vision to see that “water & food security of all Ethiopians are ensured for sustainable development and perpetuity of their livelihood.” To this end, ERHA strives for promotion of rainwater harvesting in Ethiopia through advocacy, networking, research and capacity building to its various stakeholders in developing, adapting and disseminating rainwater harvesting. Since the last few years, ERHA has been implementing various rainwater harvesting promotion and up scaling projects with its partners in different parts of the country. Currently, ERHA is looking for a competent candidate to fill the vacant post of Executive Director to run its Secretariat in Addis Ababa.

1. Position: Executive Director 2. Accountable to: ERHA Executive Board 3. Summary of Main Duties & Responsibilities:

Plans, organizes, directs coordinates and controls the activities of all functional organs at ERHA Head Office as well as future branch offices in regional states. He/she performs tasks that involve extensive policy interpretation, strategy development, financial and human resources planning and programme analysis. As a chief executive officer of ERHA, he/she is responsible for the efficient and cost effective operation of all the functions of ERHA and the fulfilment of its organizational objectives.

4. Detail Responsibilities & Activities: • Plans organizes, directs, coordinates and controls the activities of all functional organs at Head

Office as well as regional branch offices as might be needed,• Formulates ERHA’s short, medium and long term strategic objectives and policies within the

powers delegated to him/her by ERHA Executive Board,• Directs, coordinates and supervises the setting up of short and long term plans, working

programmes and budget for the function of ERHA; submits and implements the same after approval by the Executive Board,

• Ensures that all the rules, regulations, guidelines, directives and procedures of the organization are adhered to,

• Sees to it that the funds and assets of ERHA are used most economically, • Identifies sources of finance from outside, enters into contract with funding partners to meet

the organizational requirement and to provide adequate working funds for the functions of the organization,

• Approves administrative and financial requests within the powers delegated to him/her by the Executive Board,

• Maintains and establishes networking, good relationships and cooperation with national and international organizations, donors, partners and other collaborators to promote the objectives and build image and credibility of ERHA,

• Maintains adequate contact with government and non – government agencies, learning and research institutions of relevance to advance ERHA’s objectives,

• Reviews and examines auditors’ reports and submits to ERHA Executive Board with appropriate comments and recommendations as appropriate,

• Ensures that staff recruitment, placement, training, salary increment, promotion, transfers, termination and disciplinary measures are executed according to the established rules, regulations, guidelines and directives of the organization and the law of the land,

• Ensures that there is sufficient fund, skilled human power and proper organizational arrangement to carry out ERHA’s short, medium and long term objectives,

• Ensures that periodic, regular and timely reports and financial statements are prepared and submitted to the Executive Board, funding partners and other key stakeholders,

• Visits Programme areas and project sites to follow up progress of work and solve major problems on the spot, and;

• Performs other duties assigned by ERHA Executive Board.

5. Educational Background and Work Experience

The prospective Project Officer should have:

• Minimum Masters Degree in either of Agricultural Engineering, Agricultural Extension, SWC Engineering, Water Engineering, Irrigation Engineering or other related fields of natural resources management;

• At least 12 years experience with local/international NGOs or development organisations with a specific focus in project management, planning, monitoring & evaluation;

• Firsthand experience in the technical designs and supervisions, planning and implementation of RWH projects;

• Experience with strategic planning and management; including working with a diverse donor portfolio and an in-depth understanding of their project management policies and procedures;

• Experience in facilitating project monitoring, evaluation and back stopping with a diverse implementation partners at grass roots levels;

• Demonstrated leadership skills, excellent interpersonal skills and an ability to organize and motivate others;

• Demonstrated facilitation, training and communication skills;• Computer literate with a good level of working skills in operating PCs with the latest text and

data processing application software’s (e.g. MS Word, MS Excel, MS ACCESS, MS Power Point, MS Publisher, Auto Cad …);

• Knowledge of GIS is a must;• Fluent in oral and written English with very good English writing skills;• Experience in reporting and production of promotional materials (in English and local

languages) would be an asset;• Work experiences involving or directly related to the various major responsibilities indicated

for the prospective post would be advantageous;

6. Personal Qualities• Good understanding of the principles and purposes of people-centred development works; • Good inter-personal skills;• Ability to work independently and with a team with demonstrable skill and firm believer in

teamwork, participatory and objective-focused leadership style;• Ability and willingness to work under pressure;• Exposure to the theoretical bases and practical applications of techniques and tools of

participatory enquiry methods to undertake research and development for technology promotion aimed at poverty reduction such as livelihood and gender analysis, PTD, PR&D, PAR, LFA … etc;

• Kin interest for pursuing new ideas and practices, experimenting on latest innovations and working under changing situation;

• Personal interest and sense of obligation to work towards improving the lives of rural communities and a better management of the environment in order to realise a fairer world and sustainable use of natural resources.

7. Salary and Benefits

Negotiable in accordance with ERHA’s relevant packages;ERHA is an equal opportunity employer and encourages qualified women to apply.

Applicants should submit letters of application, detailed curriculum vitae and names of three professional referees by 16th November 20 11, the latest,

To: ERHA Secretariat;Zerihun Building (3rd floor, Room No.43);

Haile Gebreselassie Avenue;Wereda 17. Kebele14, H.NO. 493/43;

P.O. Box 27671/1000; Addis Ababa; EthiopiaTelephone: ++251-(0)11-663 85 13/14;Cell phone: ++251-(0)91-124 94 26;

Fax : ++251-(0)11-663 85 14;E-mail: [email protected] and/or [email protected];

Only short-listed candidates will be contacted.

DAWIT GIRMAY BUILDING CONTRACTORInvitesqualifiedapplicanttoapplyforthefollowingVacantPost.

No Title of the post Required NoRequirements

Place of work Education Experience Skill (mandatory)

1 Office Engineer 2 Bsc. Degree in Construction Technology & management OR Bsc.

3- Years & above Computer (primavera & MS Project Haramaya University & Diredawa University

2 Construction General Forman 2Diploma in building construction

4- Years & above Haramaya University

VACANCY

Interested and qualified applicants fulfilling the above requirements should send non-returnable application, C.V and relevant documents to the following AddressInfront of St. Gebriel Hospital around Glory Hotel With in 7 days from the date of this announcement Tel. Office 0116-620300 (0910040846)Fax 0116632072Only short listed applicants will be contacted for interviewSalary:- Attractive & Negotiable Dawit Girmay Building Contractor

Page 25: Reporter Issue 1201

|ገጽ 25 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

የኢትዮጵያ አርኪዮሎጂና ፓሌዎንቶሎጂ ማኅበር ዛሬ ጥቅምት 22 ቀን 2004 ዓ.ም. “ቋንቋዎቻችንና ፊደሎቻችን ከየት መጡ” በሚል ርእስ በብሔራዊ ሙዚየም አዳራሽ በ10 ሰዓት ውይይት ያካሒዳል:: ጥናቱን የሚያቀርቡት በጀርመን ማምዝ ዩኒቨርሲቲ የጥንት ጽሑፎች ተመራማሪው ዶክተር በኩረ ጽዮን ዘርዐ ዮሐንስ መሆናቸውን የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ተክሌ ሐጎስ ለሪፖርተር አስታውቀዋል::

ምን የት?

“ቋንቋዎቻችንና ፊደሎቻችን

ከየት መጡ?”

ከዚህ ሌላ ‹‹የጠፋ ይገኛል››

በጣም ደስ ይለኛል:: እኛ አገር ብዙ ጊዜ የሚያፅናና ነገር አይሰማም::

ባለው ላይ ነው የሚጨምሩት:: በሐዘን ላይ ሐዘን::

ሪፖርተር፡- ‹‹ቺጌ›› የሚለው ቺክችካንና ሬጌን አንድ ላይ በማጣመር የተሠራ ነው:: እንዴት አሰብከው?

ኃይሌ ሩትስ፡- ከሬጌ እንደመውጣታችን ያንኑ ሬጌ ሙዚቃ ነው የምንሠራው:: ብዙ ጊዜ ግን በጭንቅላቴ የማስበው እንደ ኢትዮጵያዊነቴ ሬጌ ውስጥ የተለየ ነገር ሊያሰጠኝ የሚችለውን ነበር:: ያለንን ባህል ወስጄ እዛ ነገር ውስጥ ማድረግ እንደሆነ ስላመንኩኝ ችክችካን በሀሳብ ደረጃ ከኤሊያስ መልካ ጋር አወራሁት:: እየተነጋገርንም ሠራነው:: ሙዚቃውን እሱ ቢሠራውም ሐሳቡ ግን የኔ ነው:: ሬጌውን ብደጋግመው አዲስ ነገር ሊሆን ስለማይችል የአገራችንን ባህል ይዘን ለየት ያለ ሥራ ለመሥራት ሞክረናል:: ብዙ ሰው ችክችካን ያውቀዋል:: ከአማርኛ በተጨማሪ ኦሮምኛ ዘፈኖች ስለሚሠሩበት መርጨዋለሁ::

ሪፖርተር፡- አብዛኛውን ጊዜ ሬጌ ዘፈኖች ሲዘፈኑ በቆየ ሪትም (ምት) ውስጥ ይሠራሉ:: ለምሳሌ ‹‹ዌይቲንግ ኢን ቬይን›› በሚባለው የቦብ ማርሌ ዘፈን ሪትም (ምት) ውስጥ መኖሩን መጥቀስ ይቻላል:: ያንተ ዘፈኖች ግን እንደዚያ አልተሠሩም ለምንድን ነው?

ኃይሌ ሩትስ፡- አንድ ሬጌ ዘፋኝ ሲዘፍን ቅንብሩን ብዙ አርቲስቶች ይሠሩበታል:: እኔ ዘፈኖቹን ስሠራቸው በጊታሬ ላይ እነሱን ምቶች በመጠቀም ነው:: ስቱዲዮ ውስጥ ስገባ ግን ያንን መድገም አልፈልግም:: የራሳችን ነገሮች ጨምረን ነው የምንሠራው:: አልበሞቹ ላይ ያሉትን ‹‹ጨው ለራስህ›› ከሚለው በስተቀር የጻፍኳቸው እኔ ነኝ:: ይሄኛው ግጥምና ዜማ የኤሊያስ መልካ ነው:: ግን ከኤሊያስ ጋር ብዙዎችን ግጥሞችን አብረን አርመናል::

ሪፖርተር፡-አልበሙ ይወጣበታል ከተባለበት ጊዜ በጣም ዘግይቷል ለምንድን ነው?

ኃይሌ ሩትስ፡- አንደኛ ነገር አገሪቱ ውስጥ ያለው የሙዚቃ መንገድ፣ የአሳታሚዎች ቁጥር ማነስ፣ የኮፒ ራይት ጥሰት መበራከት ሊያዘገዩት ችለዋል:: ከዚህ በተጨማሪም አልበሙ ለመዘግየቱ አንዳንድ መግለፅ የማልፈልጋቸው ችግሮች አጋጥመውኝ ነበር:: በዚያ ላይ ስቱዲዮ እንደልብ አይገኝም:: ኤልያስ ጋ ያለው ወረፋ በጣም ብዙ ነው:: ከአቅሙ በላይ የሚሆንበት አጋጣሚዎችም አሉ:: ለነገሩ ግን መቆየቱን ወድጀዋለሁ:: ተምሬበታለሁና::

ሪፖርተር፡- የአዘፋፈን ስታይል ለውጥ በዚህ አልበም ታይቷል:: ቀስ የማለት ነገር:: አንተ ግን እንደዚያ አልነበርክም:: ይሔ ነገር እንዴት መጣ?

ኃይሌ ሩትስ፡- ብዙ ሰዎች እንደጠበቁት አላገኙትም:: እኔ በፊትም በሙዚቃ ውስጥ ትርጉም ያለው ነገር፣ መልዕክቱ ጠለቅ ያለ፣ ለሰስ ያለ ነገር ደስ ይለኛል:: ዜማው ቀስ ያለ ሙዚቃ የሰውን ልብ ይገዛል:: ጠለቅ ያለ፣ ቀላል ሙዚቃ ነበር መሥራት የምፈልገው:: አልበም ብዬ ሳስብም እንደዚህ ዓይነቱን ሙዚቃ ነው የመረጥኩት::

ሪፖርተር፡-በተወሰነ መልኩ ከጃማይካዊው ታዋቂ ዘፋኝ ጃ ኪዩር ጋር የመመሳሰል ነገር አለ:: አልበምህን ስትሠራ ብዙ ሰምተኸዋል?

ኃይሌ ሩትስ፡- ዘፈን ስንጀምር ጃ ኪዩር፣ ሲዝላ፣ ሞርጋን ሄሪቴጅ፣ ሉቺያኖ የሚባሉትን ታዋቂ ዘፋኞችን የምናውቀው:: የኔ ዘፈኖች ከተሠሩ ቆይተዋል:: ጃ ኪዩር ከእስር ከመውጣቱ በፊት ነው:: እኔ ጃ ኪዩርን እወደዋለሁ:: ግን የመመሳሰሉ ነገር እንደ አጋጣሚ ሊሆን ይችላል:: እንዲያውም በጣም የምወዳቸው ሉቺያኖንና ሲዝላን ነው:: ጃ ኪዩርንም እወደዋለሁ:: ግን እሱ አብዛኛውን ጊዜ የፍቅር ዘፈኖችን ነው የሚዘፍነው ግን እኔ ጥልቀት ያለው ዘፈኖችን እመርጣለሁ::

ሪፖርተር፡- እንግሊዝኛ ዘፋኝ እንደመሆንህ መጠን እንግሊዝኛ ዘፈን ታካትታለህ ተብሎ ተጠብቆ ነበር:: ግን ከአንዳንድ ቃላት በስተቀር አላካተትክም:: እንዴት አማርኛ ብቻ ሆነ?

ኃይሌ ሩትስ፡- አስተዳደጌ በኢትዮጵያዊ መንገድ ነው::

የ“ቺጌ”ውአቀንቃኝ

ይለ ሚካኤል ጌትነት ወይም በተለምዶ ስሙ ኃይሌ ሩትስ፤ ሙዚቀኛ እሆናለሁ ብሎ አስቦም ሆነ አልሞ አያውቅም:: ‹ሩትስ ሬጌ›› የሚባለውን የአዘፋፈን ስልትን ተከትሎ ስሙን ያገኘው ኃይሌ፣

ለሬጌ ሙዚቃ ጥልቅ ፍቅር አለው:: የሙዚቃ ጉዞውን የጀመረውም የታዋቂዎቹን የጀማይካ ዘፋኞች እንደነ ሉቺያኖ፣ ሲዝላ፣ ኬፕልተን፣ ጀንትልማንና ሞርጋን ሄሪቴጅ የሚባሉ ዘፋኞችን ዘፈን በመዝፈን ነበር:: ለአሥር ዓመታትም ያህል በተለያዩ የምሽት ክበቦች የእነዚህን ዘፋኞችን ዘፈን ይዘፍን ነበር:: በቅርብ ጊዜ በወጣው አልበሙ ‹‹ቺጌ››፣ ሬጌ ሙዚቃንና የኢትዮጵያን ምት ችክችካ አንድ ላይ ለማጣመር ችሏል:: ከዚህ አልበም ውስጥ ከተካተቱት ዘፈኖች አንዱ ‹‹አባታችን ሆይ›› ሲሆን ይሄንን ዘፈን ከታዋቂዎቹ ሉቺያኖና ማይኪ ጄኔራል ጋር በመጣመር ሠርቷል::

በዓለም አቀፍ ደረጃም ተሰሚነትን ያገኘው ዘፈኑ በተለይም በጃማይካ የሬጌ የሙዚቃ ደረጃ ሰንጠረዥ በሁለተኛነት ለብዙ ጊዜ መቆየት ችሏል:: የሙዚቃ ጉዞውንና አዲሱን ሥራውን በተመለከተ ከጥበበሥላሴ ጥጋቡ ጋር ቆይታ አድርጓል::

በፓትዋ ቋንቋም ይሁን በእንግሊዝኛ ብዘፍንም ኢትዮጵያዊ የሆነ ማንነቴን ማጣት አልፈለግኩም:: እኔ የምሠራው ለኢትዮጵያዊ ነው:: ኢትዮጵያዊ ደግሞ አማርኛ ነው የሚሰማው:: እኔም የምወደው ያንን ነው:: ፓትዋ ወይም እንግሊዝኛ ብዘፍንም አማርኛ የሚገልፅልኝን ያህል ውስጤን አይገልጹልኝም:: ምናልባት ወደፊት የተወሰኑ እንግሊዝኛ ዘፈኖች የማካተት ዕቅድ አለኝ::

ሪፖርተር፡- በዚህ አልበምህም ውስጥ ከኢዮብ መኮንን ጋር ተጣምራችሁ የሠራችሁት ‹‹ያላለው›› የሚለው ዘፈን ላይ አንተና ኢዮብ ለስለስ ባለ የሬጌ አዘፋፈን ስልት ተመሳስላችኋል:: ሒደቱ እንዴት ነበር::

ኃይሌ ሩትስ፡- ይሄንን ዘፈን የሠራነው ከቴዲ አፍሮ ጋር ቢሆንም ሐሳቡ መጨረሻ ላይ አልተስማማውም:: ከኢዮብ ጋር ልንሠራው ተስማማን:: ግጥሙም ዜማውም የኔ ነው:: ይዘቱም እግዚአብሔር የሰውን ልጅ እንደፈጠረው የሚያወራ ነው:: ኢዮብ ጓደኛዬ ነው፤ ከዚህም በተጨማሪ በሙዚቃ ውስጥ ጥሩ መልዕክትን ማስተላለፍ የሚፈልግ ሰው ነው::

ሪፖርተር፡- አልበምህ ረጅም ጊዜ እንደመውሰዱ ሐሳቦችህን የለወጥክበት አጋጣሚ አለ?

ኃይሌ ሩትስ፡- አንዳንዶቹ ግጥሞች ብዙ የራስ ተፈሪያን ተፅዕኖ ነበራቸው:: እኔ የምሠራው ለኢትዮጵያውያን ነው:: ለኢትዮጵያውያን ተብሎ ታስቦ ከራስ አመለካከትና ባህል ውጪ ከተሠራ ሰው እንደ ሙዚቃ አድንቆት ሊሰማው ይችላል እንጂ ሕይወቱ አድርጐት እንደ ሌሎቹ ዘፈኖች አብሮት ሊኖር ይችላል ብዬ አላስብም:: ጃማይካውያን ለኢትዮጵያ ክብር አላቸው:: ምክንያቱም ባህላችን፣ አመለካከታችን፣ ነፃነታችን፣ ሃይማኖታችንን በማየት ነው:: እኔ ደግሞ ተወላጅ የሆንኩት የበለጠ ይሄንን ነገር ማክበር አለብኝ:: ለዛም ነው ኢትዮጵያዊ ሙዚቃ የሠራሁት ቢሆንም የትኛውም ዜጋ የሚሰማው ሙዚቃ ዓይነት ሠርተናል:: ኤልያስም ሙዚቃውን በጣም ተጠብቦበታል::

ሪፖርተር፡- ለመጻፍ የሚያነሳሳህ ነገር ምንድን ነው?ኃይሌ ሩትስ፡- እያንዳንዱ ዘፈን አጋጣሚ አለው:: እኔ ወደ

ሬጌ ሙዚቃ የተሳብኩትም በመልዕክቱ ነው:: እኔ በተአምር ዘፋኝ እሆናለሁ ብዬ አስቤም አላውቅም:: እነ ሲዝላ፣ ሉቺያኖን ስሰማ ነው እንዴ እንደዚህ ዓይነት መልዕክት ሙዚቃ ውስጥ አለ እንዴ ይሄንን ማድረግ አለብኝ ብዬ አሰብኩ:: ከዚያ በኋላ ሙዚቃ ውስጤ እንዳለ አገኘሁት:: የማኅበረሰቡ አኗኗር፣ በመንገድ ላይ የወደቀው ሰው፣ የጨነቀው፣ ደስ ያለው ሰው በአጠቃላይ ኑሮ ለመጻፍ ያነሳሱኛል:: ይሔ ነው እኔን የሚመስጠኝ ሙዚቃም ሆነ አርቲስት መሆን ከባድ ነገር ነው:: ቃሉ ያለማል፤ ቃሉ ያጠፋል:: ስለዚህ ቃሌ እንዲያጠፋ አልፈልግም:: ለምንለው ነገር እያንዳንዳችን ኃላፊነት አለብን:: ያንን ኃላፊነት በብቃት መወጣት እፈልጋለሁ:: ነገ እናልፋለን፤ ሌላም ተተኪ ይመጣል:: እኔ እንደ አርቲስትነቴ

አበርክቼ ማለፍ የምፈልገው ነገር አለ:: ሪፖርተር፡- አድማጮች የተለያዩ ስሜቶች በዘፈኖችህ ላይ

ሊኖራቸው ይችላል:: ለአንተ ግን ለየት ያለ ትርጉም ያላቸው ዘፈኖች የትኞቹ ናቸው?

ኃይሌ ሩትስ፡- ሁሉም አሪፍ ቢሆኑም ‹‹እርጅና መጣና›› የሚለው ዘፈን ብዙ ሰው ስለ እርጅና ይመስለዋል:: ጠለቅ ብሎ የሚሰማው እኔን የተሰማኝ ስሜት ይሰማዋል:: ግን ዘፈኑ እንደ ልጅ መሆን የሚለውን የልብ ንፁህነትን የሚያሳይ ነው:: ነገር ወደ ውስጤ ሲገባ ውስጤ ቆሸሸብኝ፣ አረጀብኝ፤ ለዛ ነው ልጅነቴን የፈለኩት:: ከዚህ ሌላ ‹‹የጠፋ ይገኛል›› በጣም ደስ ይለኛል:: እኛ አገር ብዙ ጊዜ የሚያፅናና ነገር አይሰማም::

ባለው ላይ ነው የሚጨምሩት:: በሐዘን ላይ ሐዘን እና ነገም ተስፋ አለን የሚል መልዕክት ይሄ ዘፈን አለው:: ሌላኛው ‹‹ሀራምቤ›› የሚለው ዘፈን በስዋሂሊ ኅብረት የሚል ትርጉም አለው:: ኅብረተሰቡ በግል አስተሳሰብ ላይ እያተኮረ ነው:: አፍሪካውያን ያ ሁሉ ሀብትና ንብረት እያለን ችግር ውስጥ ላይ ነን:: የተሰቃየነው በጣም ለብዙ ዓመት ነው:: እርስ በርስ እኛ በምንፈጥረው ግጭት የተነሳ አገራችንና አኅጉራችን እየበደልን ነው:: የግል ሐሳባችንና ልዩነታችን ተወት አድርገን አባቶቻችን ለእኛ መስዋዕት እንደከፈሉት እኛም ለመጪው ትውልድና አፍሪካ ካለችበት ችግር ለማላቀቅ አንድ መሆን

አለብን:: ሪፖርተር፡- ‹‹አባታችን ሆይ›› የሚለው ዘፈን ጃማይካ ውስጥ

‹‹ሬጌ ቶፕ 15›› አልበም ውስጥ ለብዙ ጊዜያት መቆየት ችሏል:: እንዴት ነው?

ኃይሌ ሩትስ፡- ይሔ ዘፈን የተካተተው የማይኪ ጄኔራል አልበም ‹‹ቦርን ቱ ሩል›› የሚለው ውስጥ ነው:: በጣም የሚያስደስት ነገር ነው:: ከዚህም በላይ እነዚህን ዘፋኞች በጣም የማደንቃቸው ናቸው:: ሉቺያኖን ለአምስት ደቂቃ ያህል መድረክ ላይ ማየት የምመኘው ሰው ነበር:: እዚህ በመጡበት ሰዓት የተለያዩ ቦታዎች ዘፍነዋል:: እናም በጣም የተደሰትኩበት ጊዜ ነው:: ዘፈንም ያወቅኩት በእነሱ ነው:: አስታውሳለሁ ዘፈን በጀመርንበት ጊዜ አንዱን ጓደኛየን ታያለህ ከነዚህ ዘፋኞች ጋር አብሬ እዘፍናለሁ አልኩት:: በጭራሽ ነበር ያለኝ:: እናም በአጋጣሚ ስቱዲዮ ውስጥ አንድ ላይ ሆነን አገኘን:: ሉቺያኖ እዚህ በመጣበት ወቅት እንድትዘፍንልኝ እፈልጋለሁ አልኩትና ዘፈኖቼን አሰማሁት:: እናም ይሄንን መረጠ:: አሁንም ጓደኛዬ ነው:: በጣም ትልቅና ታዋቂ ሰው ነው:: ይሄንን ዘፈን አብሮኝ የዘፈነው እኔን አክብሮ ነው::

ሪፖርተር፡- መድረክ ላይ ከሉቺያኖ ጋር መዝፈን እንዴት ነበር?

ኃይሌ ሩትስ፡- አብረን ነው የዘፈነው በሚሌኒየም አዳራሽ

ኃይለሚካኤል ጌትነት (ኃይሌ ሩትስ)

ነበር:: አንዳንዴ ቆም እያልኩ አየው ነበር:: ከሌሎችም አርቲስቶች ጋር በጥምረት አብሬ መሥራት እፈልጋለሁ::

ሪፖርተር፡- እንዴት ወደ ሙዚቃው ገባህ?ኃይሌ ሩትስ፡- በሕፃንነቴ ከሙዚቃ ጋር የተገናኘ ምንም

ነገር የለኝም:: አስታውሳለሁ አንድ ጊዜ ጓደኛዬ ካሴት ይዞ መጣና አሰማኝ:: እስካሁንም ድረስ ስሜቱ ይሰማኛል እናም ማድረግ የምፈልገው ይኼንን ነው አልኩት:: በትምህርቴ ጐበዝ አልነበርኩም፤ ሥዕል ትንሽ እሠራ ነበር:: እግር ኳስ ጐበዝ ነበርኩ፤ መብራት ኃይል ቡድን ልጀምር ጨርሼ ሙዚቃው ውስጥ ስለገባሁ አጋጣሚው ተገጣጠመና ተውኩት:: እኔ በባሕርዬ አንድ ነገር ከሰማሁ እስከ መጨረሻው ነው የምይዘው:: ብዙ ጃማይካውያን ጓደኞች አሉኝ:: ቋንቋውንም መልመድ ቀላል ነበር:: የሙዚቃ ጉዞዬ እንደዚህ እያለ ዜማ ላስታስን ባንድ ተቀላቀልኩ:: ቀጥሎም አፍሮ ሳውንድ ባንድ ጋር አብሬ መሥራት ችያለሁ:: በኋላም ቴዲ አፍሮና ከናትናኤል ኃይሌ ጋር አብረን ሠራን:: ጥሩ መንገድ ነው የመጣሁት:: በጣም ዕድለኛ ነኝ ማለት እችላለሁ:: የሙዚቃ ችሎታው እንዳለኝ አላውቅም ነበር፤ ለካስ አለኝ::

ሪፖርተር፡- አልበምህን ለማስተዋወቅ ምን ዓይነት ጥረት እያደረግክ ነው?

ኃይሌ ሩትስ፡- ኮንሰርት ከአዲካ ጋር አብረን እያሰብን ነው:: ከዚህም በተጨማሪ ሁለት ሦስት ለሚሆኑ ዘፈኖች የቪዲዮ ክሊፕ ለመሥራት እያሰብን ነው:: ‹‹እርጅና መጣና›› እና ከጆኒ ራጋ ጋር የተጣመርንበት ‹‹መንትዮቹን›› አስበናል:: ጆኒ በጣም አሪፍ ነገር ነው የሠራልኝ::

Page 26: Reporter Issue 1201

ገጽ 26|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

የአገር ውስጥ ዜና

የዓለም ዜናፍልስጥኤም የዩኔስኮ አባል መሆኗን ተከትሎ አሜሪካ በጀቷን አቋረጠች

ፍልስጥኤም የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) አባል መሆኗን በመቃወም፣ አሜሪካ ለድርጅቱ ትሰጥ የነበረውን በጀት ማቋረጧን ኤኤፍፒ ዘግቧል:: አሜሪካ ለድርጅቱ ትሰጥ የነበረው በጀት ከጠቅላላ በጀቱ ሩብ ያህሉን ይሸፍን እንደነበር ተገልጿል:: ‹‹በኖቬምበር መጀመርያ ላይ 60 ሚሊዮን ዶላር ለድርጅቱ ለመስጠት አቅደን ነበር:: ነገር ግን አሁን ይህንን ክፍያ አንፈጽምም፤›› በማለት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቪክቶሪያ ኦላንድ ተናግረዋል:: ፈረንሳይ ፓሪስ በሚገኘው የዩኔስኮ ዋና መሥርያ ቤት ውስጥ በተካሄደው ምርጫ የፍልስጥኤም የዩኔስኮ አባልነት በ107 አገሮች ዘንድ ተቀባይነትን አግኝቷል:: አሜሪካ፣ እስራኤል፣ ካናዳ፣ ኔዘርላንድና ጀርመንን ጨምሮ 14 አገሮች የተቃወሙ ሲሆን፣ 52 አገሮች ደግሞ ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል:: ፈረንሳይ ከነአሜሪካ ተለይታ ፍልስጥኤም የድርጅቱ አባል እንድትሆን መምረጧ ብዙዎችን አስደምሟል:: የፍልስጥኤም ፕሬዚዳንት ማህሙድ አባስ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአባልነት ጥያቄ በመስከረም ወር ማቅረባቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ የድርጅቱ የፀጥታው ምክር ቤት እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 11 ቀን 2011 በሚያደርገው ስብሰባ ምርጫ ሊያካሂድ ይችላል ተብሎ ተገምቷል::

የያሲር አራፋት ባለቤት በቱኒዝያ የእስር ዋራንት ተቆረጠባቸው

አሁን በሕይወት የሌሉት የቀድሞው የፍልስጥኤም መሪ ያሲር አራፋት ባለቤት ሱሃ አራፋት ከሙስና ጋር በተያያዘ በቱኒዝያ የእስር ዋራንት እንደተቆረጠባቸው ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል:: የአራፋት ባለቤት ጉዳያቸው ሊታይ የበቃው በአሁኑ ወቅት በስደት ላይ የሚገኙትን የቀድሞውን የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ቤን አሊን ጨምሮ፣ በቀድሞ ባለሥልጣናት ላይ እየተደረገ ባለው ምርመራ ግንኙነት እንዳላቸው በመረጋገጡ ነው:: ሙስና ተፈጽሞበታል ተብሎ የተጠረጠረውም ሱሃ አራፋትና የቤን አሊ ባለቤት ሌይላ ትራቤልስ በጋራ ባቋቋሙት ዓለም አቀፍ ካርትሬጅ ትምህርት ቤት ነው:: ዘገባው እንዳመለከተው የቱኒዝያ መንግሥት እ.ኤ.አ. በ2007 ለትራቤልስ ለትምህርት ቤቱ የሚሆን በሚል 1.5 ሚሊዮን ዶላር ለግሷል:: የፈረንሳይ ዜግነት ያላቸው ሱሃ አራፋት የተወለዱት በኢየሩሳሌም ሲሆን፣ በቱኒዝያ ለረጅም ጊዜ በመኖራቸው እ.ኤ.አ. በ2004 ባለቤታቸው ከሞቱ በኋላ፣ በአገሪቱ ለረዥም ጊዜ በመኖር የሚያሰጠውን ዜግነት አግኝተው እንደነበር ዘገባው ጨምሮ ገልጿል::

ኬንያ በአልሸባብ ላይ ለሰነዘረችው ጥቃት ዓለም አቀፍ ዕርዳታ ጠየቀች

በደቡባዊ ሶማሊያ በሚገኝ ካምፕ ላይ አንድ የጦር አውሮፕላን ባደረሰው የቦምብ ድብደባ የአምስት ሰላማዊ ሰዎች መገደልንና የ50 ሰዎች መቁሰልን የዕርዳታ ድርጅቶች መግለጻቸውን ተከትሎ፣ ኬንያና ሶማሊያ በአልሸባብ ሰርጐ ገቦች ላይ እየሰነዘሩት ላለው ጥቃት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲተባበራቸው ጥሪ ማቅረባቸውን የዘገበው ኒውዮርክ ታይምስ ነው:: የአፍሪካ ኅብረት ሰላም አስከባሪ ተልዕኮ ቡድን የሶማሊያን ዋና ከተማ ሞቃዲሾን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ሥር ማድረጉ ተገልጿል:: ነገር ግን ደቡባዊውን የሶማሊያ ክፍል ኬንያ ብቻዋን ከአልሸባብ ታጣቂዎች ጋር እየተፋለመችበት ትገኛለች:: ባለፈው እሑድ በአንድ የጦር አውሮፕላን በደረሰው የቦምብ ድብደባ በረሃብ እየተሰቃዩ ያሉ 7,500 ሶማሊያውያን በተጠለሉበት ካምፕ ላይ መካሄዱ ተገልጿል:: ነገር ግን የኬንያ ባለሥልጣናት ሰኞ ዕለት በሰጡት መግለጫ የቦምብ ጥቃት ማድረሳቸውን አምነው፣ ነገር ግን በስደተኞች መጠለያ ካምፕ ላይ ሳይሆን በአልሸባብ የማሠልጠኛ ካምፕ ላይ መሆኑን ገልጸዋል:: በዚህም 10 ታጣቂዎችን መግደላቸውን ተናግረዋል:: የሶማሊያ ባለሥልጣናት በበኩላቸው ኔቶ ወደ አገሪቱ በመግባት እንዲያግዛቸው እንደሚፈልጉ መግለጻቸውን ዘገባው ጨምሮ ገልጿል::

የእንግሊዝ መንግሥት በሠልፈኞች ላይ ዕርምጃ እንደሚወስድ አስጠነቀቀ

የእንግሊዝ መንግሥት የፀረ ካፒታሊስት አማፅያን ሠልፈኞች በጐዳና ላይ የተከሏቸውን ድንኳኖች በ48 ሰዓት ውስጥ ነቃቅለው ካላነሱ፣ ሕጋዊ ዕርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ ማስጠንቀቁን የዘገበው ቢቢሲ ነው:: አማፅያኑ በበኩላቸው ለሚወሰድባቸው ዕርምጃ አፀፋውን ለመመለስ መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል:: አማፅያኑ የሰፈሩበት የቅዱስ ጳውሎስ ካቴድራልና የለንደን ከተማ ኮርፖሬሽን እንዳስታወቁት፣ በአካባቢዎቹ ጎዳና ላይ የተተከሉትን 200 ያህል ድንኳኖች ለማስነሳት የሚያስችል የፍርድ ቤት ማዘዣ ለማግኘት በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው:: በለንደን እየተካሄደ ያለው ተቃውሞ ፍትሕ እንዲሰፍን፣ እውነተኛ ዴሞክራሲ እንዲኖርና ጥቂቶችን ብቻ እየጠቀመ ብዙኅኑን እየጎዳ ያለው የአገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት እንዲስተካከል የሚጠይቅ መሆኑን ዘገባው አስታውሷል:: መንግሥት ግን ይህንን ዓይነቱን እንቅስቃሴ አስቆማለሁ እያለ ነው::

በሩብ ዓመቱ ከወጭ ንግድ 753 ሚሊዮን ዶላር ተገኝቷል

ኢትዮጵያ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከወጭ ንግድ 753 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የንግድ ሚስቴርን ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል:: ገቢው የተገኘው 275.6 ቶን መጠን ያላቸው ምርቶች ለ94 አገሮች ተልከው ነው:: ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ189.6 ሚሊዮን ዶላር ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 33 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ተብሏል:: ለገቢው መጨመር ምክንያት ከሆኑት ቡና፣ ጥራጥሬ፣ የቅባት እህሎች፣ ቅመማ ቅማም፣ ሥጋ፣ የቁም እንስሳት፣ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ጫት፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ ወርቅና ሌሎች የማዕድን ውጤቶች ተጠቃሽ ሆነዋል:: ዋነኞች የአገሪቱ ምርቶች የመዳረሻ አገሮች ጀርመን፣ ሶማሊያ፣ ቻይና፣ ሱዳን፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኔዘርላንድ፣ እንግሊዝ፣ ጂቡቲ፣ ጣሊያን፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬት፣ አሜሪካን፣ ግብፅ፣ ቤልጂየም፣ ፈረንሣይ፣ ጃፓን፣ እስራኤልና ዮርዳኖስ ይገኙበታል:: በሩብ ዓመቱ ወደ ውጭ ከተላኩት ምርቶች ውስጥ 79.8 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ምርቶች መዳረሻቸው ጀርመን መሆኑ ተጠቁሞ፣ ይህም በአጠቃላይ ከተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ 11.2 በመቶ ደርሻ መያዙን ዘገባው ገልጿል::

የአረጋውያን ፖሊሲ እንዲቀረፅ ጥሪ ቀረበ

ለአረጋውያን ችግሮችና ፍላጐቶች መፍትሔ ለማስገኘት የሚያስችል የአረጋዊያን ፖሊሲ እንዲቀረፅ ጥሪ መቅረቡን የዘገበው አዲስ ዘመን ነው:: የኢትዮጵያ ብሔራዊ አረጋውያን ማኅበር እንደገለጸው፣ እስከአሁን በኢትዮጵያ አረጋውያንን የሚመለከት ፖሊሲ አልወጣም:: አረጋውያኑም ችግሮቻቸውን አስመልክቶ ድምፃቸውን የሚያሰማላቸና ጉዳያቸውን በባለቤትነት የሚመራ አካል ባለመኖሩ፣ አረጋውያንን የሚመለከት ፖሊሲ በአፋጣኝ እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል:: አብዛኞቹ አረጋውያን ከዕድሜ መግፋት ጋር በተያያዘ ለተለያዩ ጉዳቶች የተጋለጡ መሆናቸው፣ ጥቂት የማይባሉት ደግሞ የመኖሪያ ቤት፣ የአልባሳት እንዲሁም የምግብ ችግር የሚያጋጥማቸው መሆኑ ተወስኗል::

አንበሳ ባንክ ከታክስ በፊት 61 ሚሊዮን ብር አተረፈ

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማኅበር በ2002/2003 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት ከ61.8 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱን አዲስ ዘመን ዘግቧል:: በበጀት ዓመቱ የተገኘው የትርፍ መጠን ካለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ24.5 በመቶ ብልጫ አለው:: በበጀት ዓመቱ ከተገኘው አጠቃላይ ትርፍ ውስጥ 18.1 ሚሊዮን ብር ግብር መከፈሉ ተመልክቷል:: አጠቃላይ የባንኩ እሴት 1.8 ቢሊዮን ብር መድረሱም ተገልጿል:: አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማኅበር ጥር 1 ቀን 1999 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን፣ ሰባት ሺሕ የሚጠጉ ባለ አክሲዮኖችና በመላ አገሪቱ 29 ቅርንጫፎች እንዳሉት ዘገባው ጨምሮ አስረድቷል::

የሊንከን ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ተማሪዎችን አስመረቀ

የአሜሪካው ሊንከን ዩኒቨርሲቲ በአዲስ አበባ በጀመረው የማታ ፕሮግራም በንግድ አስተዳደር ዘርፍ በሁለተኛ ዲግሪ 26 ተማሪዎችን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን አዳራሽ ጥቅምት 18 ቀን 2004 አስመረቀ:: ተማሪዎቹ ለ14 ወራት ያህል ከአሜሪካ በመጡ ፕሮፌሰሮች ትምህርታቸውን መከታተላቸው ታውቋል:: ዩኒቨርሲቲው ኢትዮጵያ ውስጥ ሲያስመርቅ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን በናይጄሪያ፣ በሰርቢያ፣ በቻይና፣ በቬትናምና በካናዳ በተመሳሳይ ሁኔታ የማታ ፕሮግራሞች እንዳሉት ታውቋል:: ሊንከን ዩኒቨርሲቲ በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት ውስጥ የሚገኝ እ.ኤ.አ. በ1919 የተቋቋመ ዩኒቨርሲቲ ነው::

ለፈው ሰኞ ማለዳ በሊቢያ ሁለት አስገራሚ ክስተቶች ታዩ:: የሊቢያ አመፅ መነሻና ማዕከል በነበረችው ቤንጋዚ ፍርድ ቤት ሕንፃ ላይ የአልቃይዳ ጥቁር ሰንደቅ ዓላማ ሲውለበለብ ታየ:: ትሪፖሊ ውስጥ

ደግሞ የጋዳፊ መንግሥት ከተገረሰሰ በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ በነፃ አውጪዎቹ ተዋጊዎች መካከል ከፍተኛ ውጊያ ተደረገ:: ሁለቱም ክስተቶች ለአዲሲቱ ሊቢያ የማይስማሙ፣ ከአምባገነንነት ለመላቀቅ የተደረገውን የስምንት ወራት ትግል ትርጉመ ቢስ የሚያደርጉና ድኅረ ጋዳፊ ሊቢያን በዓለም አቀፍ ደረጃም ሆነ በአካባቢው አሳሳቢ እንድትሆን ሊያደርጋት ይችላል ተብሏል::

እንደ ቴሌግራፍ ዘገባ፣ “ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም” የሚል በዓረብኛ መግለጫ የታተመበት የአልቃይዳ ጥቁር ሰንደቅ ዓላማ፣ ከሊቢያ ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ጎን ለጎን በፍርድ ቤቱ ሕንፃ ላይ ሲውለበለብ ከታየ በኋላ የሊቢያ ብሔራዊ ሽግግር ምክር ቤት ይኼ ድርጊት እንደማይመለከተው አስተባብሏል:: የሊቢያ አብዮት የተመራባት ከተማ ውስጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ በአሸባሪነት የተፈረጀው አልቃይዳ ሰንደቅ ዓላማ መውለብለቡ፣ በሊቢያ የአክራሪነት ፍላጎት ይንፀባረቅ ይሆን ማሰኘቱን ዴይሊ ሜይል ዘግቧል::

ቮይስ ዶት ኮም ተባለው ድረ ገጽ ደግሞ የአልቃይዳን ዓርማ ያነገቡ አክራሪዎች በቤንጋዚ ጎዳናዎች ላይ በተሽከርካሪዎች ላይ ሆነው ከመታየታቸውም በተጨማሪ፣ ዓርማውን እያውለበለቡ በጩኸት፣ “ኢዝላሚያ፣ ኢዝላሚያ፣ ምዕራብና ምሥራቅ የሚባል ነገር የለም፤” ሲሉ መፈክር ማስተጋባታቸውን ገልጿል:: ሊቢያ ከምሥራቅና ከምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች በሚነሱ ተፅዕኖዎች ሥር መውደቅ ሳይኖርባት አንዲት እስላማዊት አገር ናት ማለታቸው እንደሆነ ተነግሯል::

የዴይሊ ሜይል ዘገባ እንደሚያሳየው፣ እንዲህ ዓይነቱ ስሜት መናኘት የጀመረው ጋዳፊን ሲዋጉ የነበሩት አማፂያን በያዙዋቸው ከተሞች የሸርያ ሕግን ተግባራዊ ማድረግ ከጀመሩ ወዲህ ነው:: በቅርቡም የሊቢያ ነፃ መውጣት ቤንጋዚ ውስጥ ሲታወጅ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሙስጠፋ አብዱል ጀሊል በነፃዋ ሊቢያ የሕጎች ሀሉ ምንጭ የሚሆነው የሸሪያ ሕግ ነው ማለታቸው ይታወሳል:: ምዕራባውያንንም ሆነ ለሊቢያ ነፃ መውጣት ድጋፋቸውን የሰጡትን በሙሉ ያሳሰባቸው ግን፣ በአልቃይዳ ደቀ መዝሙሮች የሚመራ የእስልምና አክራሪነት በአዲሲቷ ሊቢያ ይከሰት ይሆን የሚለው ሆኗል::

የአገሪቱ የሽግግር ምክር ቤት የአገሪቱን ሰላምና ፀጥታ ለማስፈን ውጥረት ውስጥ ባለበት በዚህ ወቅት፣ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ሲቪሎች ታጣቂ በመሆናቸው ምክንያት ችግሮች እየተከሰቱ ነው:: ባለፈው ሰኞ እነዚህ ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ታጣቂዎች በማን እንደታዘዘ የማይታወቅ ከፍተኛ ውጊያ በመክፈታቸው የትሪፖሊን ነዋሪዎች ረብሸዋል:: በዚህ ውጊያ

ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ሰባት ሰዎች ደግሞ በፅኑ ቆስለዋል::በትሪፖሊ ማዕከላዊ ሥፍራ ላይ በሚገኝ ሆስፒታል

ተኝቶ በመታከም ላይ የሚገኝ አንድ ግለሰብን ለመግደል ዚናታን ከምትባል ከተማ የመጡት ተዋጊዎች፣ ወደ ትሪፖሊ እንዳይገቡ በትሪፖሊ ብርጌድ በመከልከላቸው ነበር በቀጥታ ወደ ውጊያ የገቡት ተብሏል:: እንደ ቴሌግራፍ ዘገባ፣ በውጊያው ወቅት በሆስፒታሉ ሕንፃዎች ላይ ጉዳት ሲደርስ፣ ዶክተሮችና ነርሶች ሥራቸውን ጥለው ሸሽተዋል:: ሁለት አረጋውያን ደግሞ በድንጋጤ በተፈጠረባቸው የልብ ሕመም እንደሞቱ ተረጋግጧል:: ውጊያውም ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ ምሽት ላይ በስንት መከራ እንዲቆም መደረጉ ታውቋል::

እንዲህ ዓይነቱ ሥርዓት አልበኝነት የተከሰተው በትሪፖሊ ብቻ ሳይሆን፣ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ጋዳፊና ሠራዊታቸው ከፍተኛ እልቂት ባደረሱባት በሚዝራታ ከተማም ታይቷል:: የሚዝራታ ከተማ ታጣቂዎች በአሁኑ ጊዜ ሊቢያ ውስጠጥ ተፈሪ ከመሆናቸውም በላይ፣ ሕግና ሥርዓት ለማስጠበቅ የሚደረገውን ሙከራ በማክሸፍም ይታወቃሉ:: በቅርቡ በጎረቤት ከተማ ውስጥ የጋዳፊ ደጋፊዎች ባሏቸው ሰዎች ላይ የብቀላ ዘመቻ ማድረጋቸው በስፋት እየተነገረ ነው:: የሚዝራታ ታጣቂዎች ከማንም በላይ ራሳቸውን በመካብ በሕገወጥነት በሚወስዷቸው ዕርምጃዎች ለሽግግር ምክር ቤቱ ሳይቀር ራስ ምታት መሆናቸው ይነገራል:: ሊቢያ ከእንዲህ ዓይነቱ ውጥንቅጥ ውስጥ በጊዜ ካልወጣች የታጣቂዎችና የአክራሪዎች ምሽግ በመሆን ከድጥ ወደ ማጥ ልትገባ እንደምትችል ተሰግቷል::

ይህ በዚህ እንዳለ ላለፉት ሰባት ወራት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ይሁንታ የምዕራባውያንን ጥቅም ለማስከበር ተሰልፎ ነበር የሚባለው የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ)፣ ሰኞ እኩለ ሌሊት ላይ የሊቢያ ተልዕኮውን ማጠናቀቁን አስታውቋል:: የኔቶ ዋና ጸሐፊ አንድረስ ፎግ ራምሰንሰን በሊቢያ የተካሄደው ዘመቻ በድልና በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀው፣ ሊቢያውያን ግን አዲሱን የታሪክ ምዕራፍ መጻፍ ጀምረዋል ብለዋል:: የተሰጣቸው የተመድ ይሁንታ ሊቢያውያንን ከጋዳፊ የአየርና የምድር ጥቃት ለመጠበቅ እንጂ፣ እግረኛ ወታደር ማሰማራት እንዳልነበረም አስታውቀዋል:: ኔቶ በሊቢያ 26,000 በረራዎችን በማካሄድ በፈጸመው የአየር ድብደባ የጋዳፊን መንግሥት አየር ኃይልና የአየር መከላከል ተቋሟት ከማውደሙም በላይ፣ ጋዳፊ በተቃዋሚዎቻቸው ላይ የበላይነት እንዳይኖራቸው አድርጓል:: እስከ ሕይወታቻው ፍፃሜ ደረስ በዘመቻው በመሳተፍ የመንግሥታቸውን የመጨረሻና የተሟጠጠ ኃይል ፍርክስክሱ እንዲወጣ ረድቷል::

የኔቶ ዋና ጸሐፊ ራምሰንሰን የኔቶ ተልዕኮ ቢያበቃም፣ ወዳጅ አገሮች በተናጠል የሊቢያን ሠራዊት በማቋቋምና የድንበር ጥበቃ በማድረግ አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ እንደሚችሉ ፍንጭ ሰጥተዋል:: እነዚህ አገሮች አሜሪካ፣ እንግሊዝና ፈረንሣይ እንዲሁም አንዳንድ የባህረ ሰላጤው አገሮች ሊሆኑ እንደሚችሉ ተገምቷል:: ስድስት ሺሕ የሚጠጉ ዒላማዎችን የደበደበው ኔቶ “ኦፕሬሽን ዩኒፋይድ ፕሬቴክተር” በሚባል የኮድ ስያሜ የሚታወቀውን ዘመቻውን ሲያቆም፣ በሊቢያ መሬት ላይ የሚታየው ሥርዓተ አልበኝነትና ጽንፈኝነት ምዕራባውያንን እያሳሰበ ነው:: የሽግግር ምክር ቤቱም ይህ ጭንቀት የገባው ይመስላል::

ባለፈው ሰኞ ምሽት በተካሄደው ምርጫ የሽግግር መንግሥቱን በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንዲመሩ ምሁሩ አብዱልራሂም አል ኪብ ተመርጠዋል:: ከሽግግር ምክር ቤቱ 51 ድምፆች 26 በማግኘት በጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስትርነት የተመደቡት አል ኪብ፣ ከትሪፖሊ፣ ከደቡብና ከሰሜን ካሮላይና ዩኒቨርሲቲዎች የተለያዩ ዲግሪዎችን ያገኙ ሲሆኑ፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬት ፔትሮሊየም ኢንስቲቲዩትን ጨምሮ በበርካታ ኮሌጆች ማስተማራቸው ታውቋል:: በኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ ተመራማሪ የነበሩት አል ኪብ፣ በርካታ የጥናት ጽሑፎችን የጻፉ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል::

ጠቅላይ ሚኒስትር አል ኪብ የሊቢያን ሰላምና ፀጥታ ማስፈን ዋነኛው ሥራቸው እንደሚሆን ያስታወቁ ሲሆን፣ ከሁሉም በላይ ግን ሰብዓዊ መብትን ማስከበር ቀዳሚ አጀንዳቸው እንደሚሆን ከተመረጡ በኋላ ገልጸዋል:: “የምንገነባት አገር ሰብዓዊ መብትን የምታከብር መሆን አለባት:: በምንም ዓይነት ሁኔታ የሰብዓዊ መብት መጣስን አንታገስም:: ለዚህም ጊዜ ሊኖረን ይገባል፤” ብለዋል::

በአሁኑ ጊዜ በየቦታው ትጥቅ ካነገቱትና በትጥቅ ትግሉ ጊዜ የጋዳፊን መንግሥት ከተዋጉት ግለሰቦችና ቡድኖች ጋር የአገሪቱን ሰላም ለማስፈን ሲባል አብረው እንደሚሠሩ አስታውቀው፣ “አብዮተኞቹና ተዋጊዎቹ ወንድሞቻችን የሊቢያን ሰላም ለማስፈን ያላቸውን ፍላጎት እናውቃለን፤ ስለዚህም አብረን ይህንን እንወጣለን፤” ማለታቸው ተዘግቧል::

በመጪዎቹ ስምንት ወራት ውስጥ የአገሪቱን ሕገ መንግሥት ለማርቀቅና 200 መቀመጫዎች የሚኖሩትን የሊቢያ ብሔሪዊ ሸንጎ ለመመሥረት የሚያስችለውን ምርጫ ለማዘጋጀት፣ የሽግግር መንግሥቱ ከአዳዲሶቹ አሳሳቢ ክስተቶች የሚያገኘው ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል ከሚለው በተጨማሪ፣ በድኅረ ጋዳፊ ሊቢያ ሊያጋጥም የሚችለውን ችግር ከወዲሁ መገመት አዳጋች መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች እየተናገሩ ነው::

ሊቢያ አሳሳቢ ሆናለች

ድኅረ ጋዳፊ

ባለፈው ሰኞ እነዚህ ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ታጣቂዎች በማን እንደታዘዘ የማይታወቅ ከፍተኛ ውጊያ በመክፈታቸው የትሪፖሊን ነዋሪዎች ረብሸዋል

Page 27: Reporter Issue 1201

|ገጽ 27 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

ሪፖርተር፡- ለኢንቨስተሮች በሚሰጡ ሰፋፊ መሬቶችና የምግብ ዋስትናን በተመለከተ አንድ ጥናት አቅርበዋል:: ለባዮ ፊውልና ለእህል ልማት የሚውሉ መሬቶች በሔክታር ምን ያህል መሆን እንዳለባቸው የሚያስቀመጥ መመርያ እየተጣሰ እንደሆነ ይታያል:: ለመሆኑ መመርያው ተግባር ላይ ውሏል?

አቶ ደሳለኝ፡- በአንድ በኩል ውሏል ማለት ይቻላል:: ክፍያን በተመለከተ ከዚህ በፊት የነበረው የመሬት ኪራይ በጣም አነስተኛ ነበር:: ከዚህ በፊት ኪራዩንም የሚወስኑት የክልል መስተዳድሮች ነበሩ:: እንደ እ.ኤ.አ ከ2008 በፊት የክልል መስተዳድሮች ሙሉ ኃላፊነት ነበራቸው:: ስለዚህ አንድ ኢንቨስተር ለሚመለከተው የክልል መስተዳድር አመልክቶ መሬት ማግኘት ይችላል:: የኪራዩን መጠን ክልሎች ነበሩ የሚያወጡት:: ተመኑንም እያንዳንዱ ክልል በራሱ የመሬት አዋጅ አማካይነት ያስቀምጣል:: የፌዴራሉ የግብርና ሚኒስቴር ኃላፊነቱን ከአራት ዓመታት በፊት ሲቀበል ከ5000 ሔክታር በላይ መሬቶችን በፌዴራል ለማስተዳደር ነበር:: አሁን በቅርቡ ደግሞ የሁሉንም መሬቶች ኃላፊነት ጠቅልሎ መውሰዱ ይነገራል:: ሆኖም ለማረጋገጥ ሞክሬ አልቻልኩም እንጂ ከ5000 ሔክታር በታች ያሉትም በግብርና ሚኒስቴር ኃላፊነት ሥር እንደሆኑ የሚሰማ ነገር አለ::

ሪፖርተር፡- ለፌዴራሉ መንግሥት የተሰጡበት ምክንያት ምንድን ነው?

አቶ ደሳለኝ፡- አንድ ወጥ አመራር፣ ቅልጥፍናና የተሻለ አገልግሎት ኖሮ ኢንቨስተሮችን ለማስተናገድ የሚሉ ምክንያቶች አሉ:: ይኼ ሆኖ ሳለ የኪራይ ክፍያው ግን እንደነበር ነው:: በቅርቡ ካልተሳሳትኩ አምና ነው የግብርና መመርያ የወጣው:: መመርያው ለክልሎች የአጠቃቀም ሐሳብ ለመስጠት የወጣ ነው:: ራሱ የፌዴራሉ ግብርና ሚኒስቴር መመርያውን ሥራ ላይ ማዋል የጀመረው አሁን በቅርቡ ነው:: ተመኑ በሥራ ላይ ውሏል:: ከአዲስ አበባ እየራቀ ሲሄድ የመሬት ዋጋ እየቀነሰ ይሄዳል ይላል:: ለምሳሌ ጋምቤላ ላይ በሔክታር 158 ብር በዓመት ይከፈላል:: በፊት ከ30 እስከ 35 ብር ነበር::

ሪፖርተር፡- ሆኖም ግን መሬት ለኢንቨስትመንት በሚሰጥበት ጊዜ መመርያውን ባወጣው በራሱ በግብርና ሚኒስቴር ሕግ እንደሚጣስ በጥናትዎ አስቀምጠዋል:: ለሰብል የሚፈቀደውን 20 ሺሕ ሔክታርና ለባዮ ፊውል የተፈቀደውን 50 ሺሕ ሔክታር መሬት በመጣስ አንዳንድ ኢንቨስተሮች በገፍ ወስደዋል ተብሏል:: የዚህን ጉዳት እንዴት ያዩታል?

አቶ ደሳለኝ፡- ይህ እንግዲህ ራሱ የፌዴራል ግብርና ሚኒስቴር ያወጣውን ደንብ አለማክበሩን እኮ ነው የሚያሳየው:: ሌላ ምን ይባላል? ራሱ ያወጣውን ሕግ በሥራ ላይ አላዋለውም::

ሪፖርተር፡- ምናልባት ተግባራዊ የሚያደርግበት ጊዜ ላይ ስላልደረሰ ይሆን?

አቶ ደሳለኝ፡- በሥራ ላይ ለማዋልማ እየተሞከረ ነው:: የኪራይ ዋጋ ለምሳሌ ሥራ ላይ እየዋለ ነው:: ሌሎቹ ሁኔታዎች ግን እንዴት እየተሠራባቸው እንደሆነ ለማወቅ አልተቻለም:: ጥናቱን ያካሄድኩት ባለፈው ዓመት ነው:: በዚያን ጊዜ የፌዴራል ግብርና ሚኒስቴር መመርያውን በሥራ ላይ አላዋለም ነበር:: ከዚያ ወዲህ ግን የተሻሻለ ነገር ስለመኖሩ መመለስ ያለበት ራሱ ግብርና ሚኒስቴር ነው::

ሪፖርተር፡- ከውጭ ኢንቨስተሮች ጋር በተያያዘ በጥናትዎ ከተገኘው ጥቅም ይልቅ ጉዳቱ እንደሚያመዝን ተጨባጭ እውነታዎች እንዳሉ ገልጸዋል:: የደረሱት ጉዳቶች ምን ምን እንደሆኑ ቢጠቃቅሱልን?

አቶ ደሳለኝ፡- የአካባቢ ችግሮችን አስከትሏል:: ገበሬዎችን ስናናግራቸው የተረዳነው እፅዋቶቻቸው እየጠፉባቸው መሆኑን

ተረድተናል:: ዛፎች እየተቆረጡ ነው:: በረጅም ጊዜ ሒደት ለአካባቢ አደጋ የሚፈጥር አካሄድ እየታየ ነው:: ወደፊት የሚያሰጋን ነገር ትልልቆቹ ኢንቨስተሮች በእርሻቸው አካባቢ አግሮ ኬሚካሎችን መጠቀማቸው አይቀሬ መሆኑን ነው:: እንደኛ ገበሬ በተፈጥሮአዊ መንገድ የሚያርሱ አይደሉም:: አግሮ ኬሚካሉ ውሎ ሲያድር ውኃ ውስጥ ሰርጎ እየገባ ብዙ ጉዳት የማድረሱ ነገር አሳሳቢ ነው::

ሪፖርተር፡- አንዳንድ ኢንቨስተሮች ለአብነት ካሩቱሪ ለሚዲያዎች ሲናገር እንደሰማነው የተሰጠው መሬት ማዳበሪያ ሳያስፈልገው የሚታረስ መሆኑን ነው::

አቶ ደሳለኝ፡- በጊዜ ሒደት ማዳበሪያ መጠቀሙ አይቀሬ ነው:: ከአንድ ዓመት በኋላ ሊታይ የሚችል ነው:: ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ሲባል ማዳበሪያ መጠቀም ይመጣል::

ሪፖርተር፡- በጥናቱ የታየው አንኳር ጉዳይ የውጭ ኢንቨስተሮች ያገኙትን ትርፍና ገቢ ወደ አገራቸው መውሰድ እንደሚችሉ ነው:: በውጭ ምንዛሪ ያገኙትን ገቢ በሙሉ መውሰድ ተፈቅዶላቸዋል ማለት ነው?

አቶ ደሳለኝ፡- የኢንቨስትመንት አዋጁ እንደዚያ ነው የሚለው::

ሪፖርተር፡- የአገሪቱ ጥቅም ታዲያ የቱ ጋ ነው? ምንድን ነው የአገሪቱ ትርፍ?

አቶ ደሳለኝ፡- እኔም አሳሳቢ ያልኩት ይህንኑ ነው:: ሊገባኝ አልቻለም:: አንዳንድ ኢኮኖሚስቶቻችንን ጠይቄያለሁ:: ጥቅሙ የት ጋ እንደሆነ ግራ ገብቷቸዋል:: አብዛኞቹ መሬት የያዙት ሰዎች ዛሬውኑ የግብርና ውጤት አይኖራቸውም:: ግብርና ጊዜ ይወስዳል፤ ብዙ ሊመቻችለት የሚገባ ነገርም ይኖራል:: የሚስተካከሉ ነገሮች ብዙ አሉ:: እስካሁን ድረስ ትልልቆቹ አምራቾች አምርተው ወደ ገበያ አላወጡም:: ሳዑዲ ስታር በዚህ ዓመት ወደ ወጭ እልካለሁ ብሎ ነበር:: እውነትም ደርሶለት እንደሁ ለማወቅ አልቻልኩም:: ካሩቱሪም እልካለሁ ሲል ነበር:: የዘራው ምርት በጎርፍ እንደተበላ አስታውቋል:: ባኮ ላይ ያለው ምርቱም በአረምና በጎርፍ ተበልቷል:: እንግዲህ እነዚህ ሰዎች ያገኙትን ገንዘብ ወደ ውጭ ይልኩታል? አሊያም ምን ያደርጉታል? የሚለው የሚታወቀው ከአምስት ዓመት በኋላ ሊሆን ይችላል:: አሁን ግን ያንን መገመት አስቸጋሪ ይሆናል::

ሪፖርተር፡- በአብዛኛው የተሰጣቸው መሬት አነስተኛ ገበሬዎች የነበሩበት ወይም ደግሞ ደን የነበረ መሆኑ ይነገራል:: ኩባንያዎቹ የምግብ እጥረት ወዳሉባቸው አገሮቻቸው ኤክስፖርት እንደሚያደርጉም ግልጽ ነውና በአገሪቱ የምግብ ዋስትና ላይ ተፅዕኖ አያመጣም?

አቶ ደሳለኝ፡- ይኼ እጅግ አሳሳቢ ነው:: መንግሥት

ባወጣው የኢንቨስትመንት አዋጅ ኤክስፖርት ይበረታታል:: ብዙ ኤክስፖርት ካደረግህ ብዙ ጥቅም ታገኛለህ:: የፋይናንስ ማበረታቻ ይሰጥሀል:: ስለዚህ አምርተው ወደ ውጭ የሚልኩ ይበረታታሉ:: ግብርና ሚኒስቴር መሬቱን ሲሰጣቸው የውጭ ምንዛሪ ላይ በማተኰር ነው:: መንግሥት የሚለው የውጭ

ምንዛሪ እናገኝበታለን ነው:: ሪፖርተር፡- ግን እኰ የውጭ

ምንዛሪውንም መውሰድ ይችላሉ:: ተፈቅዶላቸዋል::

አቶ ደሳለኝ፡- ይችላሉ:: በአዋጁ መሠረት ይችላሉ:: እኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ለማነጋገር ሞክረን አልተሳካልንም:: እናንተ ጥቅሙ የቱ ጋ እንደሆነ ብታነጋግሯቸው ጥሩ ነው:: ነገር ግን አንዱ የውጭ ምንዛሪ ይገኝበታል የሚባለው የመሬቱን ኪራይ መክፈላቸው ነው:: እርግጥ ለአምስት ዓመትና ለመሳሰለው ሁሉ የእፎይታ ጊዜ ይሰጣቸዋል:: ሲከፍሉ ግን መንግሥት ያንን ይምራቸዋል ወይም ይተውላቸዋል ማለትም አይደለም:: የመክፈያ ጊዜያቸው ሲደርስ ለእፎይታ የተሰጣቸውንም ደምረው ይከፍላሉ:: የገንዘብ ምህረት አልተሰጣቸውም፤ ጊዜው ተራዘመላቸው እንጂ::

ሪፖርተር፡- ከታክስ ነው ማለት ነው መንግሥት የውጭ ምንዛሪ የሚያገኘው?

አቶ ደሳለኝ፡- የመሬቱን ኪራይ መክፈል ሲጀምሩ

ገንዘቡን ካገራቸው አምጥተው ይሁን ወይም ከሌላ ምንጭ ግልጽ አይደለም:: በሌላ በኩል ግን መንግሥት ራሱ ኢንቨስተሮች ከአገር ውስጥ ባንኮች መበደር እንደሚችሉ አስቀምጧል:: ስለዚህ ካሩቱሪ ዘንድሮ 50 ሺሕ ሔክታር ላልማ ቢል ከባንክ በብር መበደር ይችላል ማለት ነው:: ሌላው ነጥብ ኢንቨስተሮች ሁለት ዓይነት መሆናቸው ነው:: አንዳንዶቹ ከመካከለኛው ምሥራቅ፣ ለአብነት ሳዑዲ ስታርን ስናይ ከመሠረታቸው አምርተው ወደ አገሮቻቸው ለመላክ የመጡ ናቸው:: አንዳንዶቹ አምርተው ወደ ዓለም ገበያ የሚያወጡ ናቸው:: ህንዶች በሩዝ ምርት ራሳቸውን ችለው ተርፏቸው ወደ ውጭ ይሸጣሉ:: ስለዚህ ካሩቱሪ እዚህ ሩዝ አምርቶ ህንድ ወስዶ ላይሸጥ ይችላል:: ነገር ግን ሕንድ በዘይት እህሎች፣ በጥራጥሬ ምርቶች፣ በአኩሪ አተር እጥረት ስላለበት ወደዚያ እንደሚልክ ይታሰባል:: በአጠቃላይ ምርቱ እዚህ ቢመረትም የሚወጣ ነው ማለት ነው:: ባዮፊውል የሚያመርቱት ላይ ያለው ዝንባሌ ምርቱ ከተገኘ በኋላ እዚሁ ይሸጣል የሚል ነው:: እስካሁን ግን ይህንን ለማድረግ የቻለ የለም:: ምርቱን ወደ ባዮፊውል ቀይሮ እዚህ ይሽጠው፣ ለውጭ ገበያ ያውጣው የታወቀ ነገር የለም:: በምርቱ ሒደት ገና በሰብል ደረጃ ሳለ ችግር እየገጠማቸው ነው:: ለምሳሌ ጃትሮፋ መጤ ነው:: እዚህ አገር አይታወቅም ነበር:: ጃትሮፋ ለዚህ አገር

መሬት ይስማማ አይስማማ፣ አዋጪ መሆኑ ገና አልታወቀም:: ያዋጣል በሚል ግምት የተገባበት ነው:: ሌላው የጉሎ ተክል እዚህም ያለ ቢሆን በኢንዱስትሪ ደረጃ ተመርቶ ባዮፊውል ወጥቶበት ገና አልተጀመረም:: በኢንዱስትሪ ደረጃ ለባዮፊውል መድረሱም ገና አልታወቀም:: አንዳንዶቹ በራሳቸው ተክለው፣ ሌሎቹ ደግሞ ገበሬው እንዲተክለው አድርገው እንገዛዋለን በማለት እያመረቱት ቢሆንም፣ ጥቅሙ ምን ያህል እንደሆነ ገና አይታወቅም::

ሪፖርተር፡- በጥናቱ ባዮፊውል ለአገር ውስጥ ፍጆታ እንደሚውል አረጋግጣችኋል?

አቶ ደሳለኝ፡- ኢንቨስተሮች አምርተው የትም መሸጥ መብታቸው ነው:: እዚህ ወይም እዚያ ሽጡ ተብሎ ገደብ አልተቀመጠም:: መንግሥት ለአገር ውስጥ ፍጆታ መዋል ያለበትን ለይቶ እንዲመረት ቢያደርግና ምርት እዚህ እንዲቀር ቢያደርግ ጥሩ ይሆን እንደነበር ጥናቱ አመልክቷል:: መንግሥት ካመረታችሁት ይህንን ያህል በመቶውን አገር ውስጥ ሽጡ ቢል ኑሮ፣ ለምግብ ዋስትናችን ጥሩ ይሆን እንደነበር ጥናቱ ያመላክታል:: ይኼ ግዴታ ግን የለባቸውም::

ሪፖርተር፡- ጥናቱ ያያቸው በዋናነት የእህልና የባዮፊውል ምርቶች ላይ ኢንቨስትመንት እየተካሄደ መሆኑን ነው::

አቶ ደሳለኝ፡- ኢንቨስትመንቱ ሦስት ዓይነት ዘርፎች ላይ እየተካሄደ ነው:: አንዱ የምግብ እህል ነው:: ትኩረቱም በሩዝና በቅባት እህሎች ላይ ነው:: አንዳንድ ጥራጥሬዎችንም ይጨምራል:: ሁለተኛው ባዮፊውል ነው:: የምግብ እህልም ለባዮፊውል እንደሚውል በቆሎ ተጠቃሽ ነው:: ሦስተኛው የኢንዱስትሪ ሰብሎች የሚባሉትን የሚመለከት ነው:: የሸንኰራ አገዳና ጥጥ ይጠቀሳሉ:: ጥጥ አምርቶ እዚህ ፋብሪካ ካለው ለግብዓትነት ይጠቀምበታል:: ወደ ውጭ እልከዋለሁ ካለም አይከለከልም:: የግብርና ሚኒስቴር የኮንትራት ውሉ ላይ እንዳሰፈረው አምራቹ ያመረተውን ምርት ምን እንደሚያደርግ ሙሉ መብትና ውሳኔ የራሱ የኢንቨስተሩ እንጂ የመንግሥት አይደለም::

ሪፖርተር፡- በእኛ አገር የኢንቨስተሮቹ አትኩሮት ከምግብ ሰብል ወይም ከባዮፊውል ወደየትኛው ያመዘነ ነው? አኃዞችስ ሊቀርቡበት ይችላሉ?

አቶ ደሳለኝ፡- አኃዝ ለማግኘት ስንሞክር የፌዴራል ግብርና እ.ኤ.አ ከ2008 በኋላ የሰጣቸውን የኢንቨስተሮች ጉዳይን ብቻ ነው የያዘው:: ከዚያ በፊት ያለውን ክልሎች በራሳቸው ስለሰጡ የእነርሱ መረጃ የለውም:: ሆኖም ግብርና ሚኒስቴር ካለው መረጃ ስንነሳ በብዛት ያተኰረው የኢንዱስትሪ ሰብሎች ላይ ነው:: ይህም ሆኖ ገና በግልጽ የታወቀ አይደለም::

ሪፖርተር፡- መንግሥት በኢትዮጵያ የመሬት ሽሚያ እንደሌለ ሽንጡን ገትሮ ይከራከራል:: በቅርቡም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን አስረግጠው ተናግረዋል:: አገሪቱ ካላት መሬት አኳያ እዚህ ግባ የማይባል መሬት ለውጭ ባለሀብቶች መሰጠቱን ተናግረዋል:: ጥናትዎን መሠረት አድርገው እንዴት ይመለከቱታል? እውነት የመሬት ሽሚያ ኢትዮጵያ ውስጥ የለም?

አቶ ደሳለኝ፡- በቃላት መጫወትና መጣላት ጥቅም የለውም:: ትልልቅ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ትልልቅ መሬት ተሰጥቷቸው ኮንትራት ፈርመው እየተንቀሳቀሱ ነው:: ይህንን እንግዲህ የመሬት ሽሚያ እንበለው ወይም የግብርና መሬት ኢንቨስትመንት እንበለው (የዓለም ባንክ እንደሚለው)፣ የግብርና ማስፋፋት፣ ዘመናዊ ኢንቨስትመንት፣ የቱ መባል እንዳለበት

ወደ ገጽ 33 ዞሯል

‹‹የመሬት ኢንቨስትመንቱ የእዚህችን አገር የምግብ ዋስትና አያረጋግጥም››

አቶ ደሳለኝ ራህመቶ፣ ተመራማሪ

በዓለም ዙሪያ መነጋገሪያ መሆን የጀመረው ‹‹የመሬት ሽሚያ›› በአገራችንና በአፍሪካም ብዙዎችን እያሳሰበ ነው:: ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች በመጉረፍ ላይ ያሉ ኩባንያዎች በተለይ አፍሪካን የትኩረታቸው ማዕከል አድርገዋታል:: በርካታ የመካከለኛው ምሥራቅና የሩቅ ምሥራቅ አገሮች ኩባንያዎች በ22 የአፍሪካ አገሮች ውስጥ እጅግ ሰፋፊ መሬቶችን

የምግብ ምርቶችንና ባዮፊውል ለማምረት እየወሰዱ ነው:: ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ አገሮች የውጭ ኩባንያዎች መዳረሻ ሆነዋል:: የአብዛኞቹ አገሮች ሕዝቦች ተጎጂዎች እየሆኑበት ነው በሚባለው በዚህ ጉዳይ ላይ በቅርቡ ጥናታቸውን ያወጡት የማኅበራዊ ጥናት መድረክ ተመራማሪው አቶ ደሳለኝ ራህመቶ፣ ይህንን እንቅስቃሴ የመሬት ኢንቨስትመንት ማለት እንደሚመርጡ፣ ነገር ግን መንግሥት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማድረግ እንዳለበት ይጠቁማሉ:: ይህ የመሬት ኢንቨስትመንት ለአገሪቱ የምገብ ዋስትና ፋይዳ አይኖረውም የሚሉትን አቶ ደሳለኝ ኃያል ዓለማየሁ አነጋግሯቸዋል::

በቃላት መጫወትና መጣላት ጥቅም የለውም:: ትልልቅ

ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ትልልቅ መሬት ተሰጥቷቸው

ኮንትራት ፈርመው እየተንቀሳቀሱ ነው:: ይህንን እንግዲህ የመሬት ሽሚያ እንበለው ወይም የግብርና መሬት ኢንቨስትመንት እንበለው (የዓለም ባንክ እንደሚለው)፣ የግብርና ማስፋፋት፣ ዘመናዊ ኢንቨስትመንት፣ የቱ መባል

እንዳለበት ምናልባት የጋዜጠኞች ወይም የሌሎች ጉዳይ ነው:: ሁኔታው ግን አለ:: የመሬት ሽሚያ የሚለውን ቃል እኔ

አልወደውም:: ለምን ቢባል ገና ቁምነገሩ ላይ ሳንነጋገር ወደ

ፀብ ስለሚያመራን ነው:: ነገሩን በደንብ እንየውና እንመርምረው::

Page 28: Reporter Issue 1201

ገጽ 28|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያፓራሜድ የቢዝነስና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከዚህ በታች በተገለፁት ክፍት የስራ ቦታዎች ብቁ ባለሞያዎችን ቀጥሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በወጣ ሰባት /7/ የስራ ቀናት ውስጥ አስፈላጊው የትምህርት ማስረጃ በፖ.ሣ.ቁ. 62 አርባምንጭ ብላችሁ መላክ ትችላላችሁ፡፡

1ኛ/ የሰርቬይንግ መምህር

ተፈላጊ ችሎታ፡- በሰርቬይንግ ወይም በተመሳሳይ ሞያ የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው የስራ ቦታ፡- አምርባምንጭ ደመወዝ፡- በስምምነት /ማራኪ/ብዛት፡- አራት

2ኛ/ የኮምፒውተር ኔትወርኪንግና ጥገና መምህር

ተፈላጊ ችሎታ፡- በኮምፒዩተር ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ ኖሮት በኮምፒዩተር ኔትወርኪንግና ጥገና በቂ ክህሎት ያለው

የስራ ቦታ፡- አምርባምንጭ ደመወዝ፡- በስምምነት /ማራኪ/ብዛት፡- አራት

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911386394/0911867149 ወይም በ046 881 2574 መደወል ይቻላል፡፡

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያየአዲስ አበባ ውሃና ሳኒቴሽን ልማትና ማስፋፊያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት

ከዚህ በታች በተገለፀው ክፍት የሥራ መደብ ብቁ ሠራተኞችን አወዳድሮ በኮንትራት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

ተ.ቁየሥራ መደብ

ዝርዝርየትምህርት ደረጃ

አግባብ ያለው የሥራ ልምድ

ብዛት

1 ጉዳይ አስፈፃሚ ዲፕሎማ በማኔጅመንት /በህግ

4 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ያለው/ያላት እና በሞተር ማሽከርከር መንጃ ፈቃድ ያለው/ላት

1

የስራ ቦታ፡- አዲስ አበባ የቅጥር ሁኔታ፡- ኮንትራት ሆኖ እንደሁኔታው የሚታደስ ደመወዝ፡- በድርጅቱ ስኬል መሠረት

የምዝገባ ቦታ፡- ከላይ ለተጠቀሰው ክፍት የሥራ መደብ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስር ተከታታይ የሥራ ቀናት ተገቢውን የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃዎቻችሁን ዋናውን ከማይመለስ ፎቶኮፒ ጋር በማያያዝ በአዲስ አበባ የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የውሃና ሳኒቴሽን ልማትና ማስፋፊያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ከመገናኛ ድልድይ ወደ ሲ.ኤም.ሲ በሚወስደው መንገድ 250 ሜትር አለፍ ብሎ የወረዳ 9 አስተዳደር ጽ/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው ቢሮአችን በአካል በመቅረብ ወይም በፖስት ሳጥን ቁ. 1436/1110 በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

Vacancy AnnouncementSave the Children Sweden, Ethiopian Country program Office would like to invite qualified applicants to apply for the following vacant positions:Position 1 .Refugee project ManagerQualificationsRequired:• BA Degree in sociology, psychology and related fields• A minimum of Five years Relevant experience• Excellent command of written and spoken English, and report writing skills• Excellent Interpersonal Skill• Experience in working in the area of child protection• Willingness to work in hardship areas

Duty station: Sherkoleand TongoRefugee camps (Beneshangule Regional State)Main Duties and Responsibilities:• Designs and develops new projects, prepare strategic documents, concept papers and

proposals, and organize midterm plan review and evaluation.• Ensures that program objectives and activities are in line with the context of Save the

Children Sweden values, aims and objectives. • Plays a key role in coordinating, supervising and monitoring child protection related

program activities and responses in coordination with Save the Children Sweden partners. • Responsible for identifying needs and resources and suggesting program recommendations

for the emergency response in line with Save the Children national and global priorities. • Monitor / reviewactivities to ensure strict conformity of program activities with Save the

Children policies and procedures • Produce high quality, analytical reports and submit to the country office on a regular basis • Monitoring the implementation of grant budgets and ensuring that corrective actions are

taken as deemed necessary• Attend meetings and conferences representing Save the Children Sweden • Carry out additional tasks as required

Salary and Benefits• Salary and Benefits will be according to the organization’s scale

Terms of employment:• One year with possibility of extension

Required Number:One

Position 2.Child protection in Emergencies OfficerQualifications Required:• BA Degree in sociology, psychology and related fields• Minimum of three years relevant work experience• Excellent command of written and spoken English• Experience in working in refugee situation in the area of child protection• Excellent Interpersonal Skill• Willingness to work in hardship areas

Duty station:Sherkole Refugee camp (Beneshangule Regional State)Main Duties and responsibilities:• Prepares annual plan, implement and monitor project activities and ensure that program

objectives and activities are in line within the context of Save the Children Sweden values, aims and objectives.

• Ensures that all children at risk in Save the Children Sweden operating areas are protected and integrated in schools, and child and youth focus activities.

• Have a key role in coordinating and supervising child protection related activities and responses in coordination with Save the Children Sweden partners

• Produce and submit quality and analytical periodic reports to Save the Children Sweden and partner organizations

• Shares information on the progress and challenges of the program work with Save the Children Sweden program staff

• Identifies capacity building training needs for Save the children Sweden staff and stake holders on child protection issues

• Carry out additional tasks as required

Salary and Benefits• Salary and Benefits will be according to the organization scale

Terms of employment:• One year with possibility of extension

Required No: Two

Interested and qualified applicants with the above requirements should submit non-returnable application, CV and copy of relevant documents in person or send to the following address within Ten days from the first date of this vacancy announcement.

Address:Save the Children Sweden, Mekanisa, on the way to Selam Nurses College. Tel. 0113210960 Email: [email protected] POBox.3457 Addis Ababa

Qualified female applicants are highly encouraged to apply

1.

Page 29: Reporter Issue 1201

|ገጽ 29 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

Page 30: Reporter Issue 1201

ገጽ 30|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004 ማህበራዊ ማህበራዊ

የኢትዮጵያ ጥራጥሬ ቅባት እህሎችና ቅመማቅመም አዘጋጅቶ ላኪዎች ማኅበር አባላት በሙሉ

የጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ ጥሪየማኅበሩ ጠቅላላ ጉባዔ የፊታችን ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በንግድ ሚኒስቴር 2ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው

የስብሰባ አዳራሽ ይከናወናል፡፡

ስለዚህ የማኅበሩ አባላት በሙሉ ከላይ በተጠቀሰው ዕለት በስብሰባው ላይ እንዲገኙ የማኅበሩ የሥራ አመራር ቦርድ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

የዕለቱ የመወያያ አጀንዳዎችም የሚከተሉት ዐቢይ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ መስጠት ይሆናል፡፡

1. የ2003 ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2004 ዕቅድና መርሀ-ግብር ገምግሞ ማጽደቅ፡፡

2. በውጭ ኦዲተር በሚቀርበው የማህበሩ የ2003 በጀት ዓመት የሂሣብ ምርመራ ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፡፡

3. አዲስ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ምርጫ ማከናወን፡፡

4. ሌሎች በአባላቱ የሚነሱ አስቸኳይ ጉዳዮች ላይ መወያየት ይሆናል፡፡

ስለሆነም የማኅበሩ አባል የሆናችሁ የዘርፉ ላኪዎች በሙሉ (ተወካዮች በአባሉ የተፈረመ የውክልና ደብዳቤ እሰከ ጥቅምት 27 ቀን 2004

ዓ.ም. ባሉት ቀናት ውስጥ በማኅበሩ ጽ/ቤት በአካል በመገኘት ኦሪጅናሉን ማስረከብ ያስፈልጋል) በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በንግድ ሚ/ር አዳራሽ

በሚከናወነው ስብሰባ ላይ እንድትገኙ የኢፖስፒያ የሥራ አመራር ቦርድ ጥሪውን ከአደራ ጭምር ያስተላልፋል፡፡

የኢፖስፒያ የሥራ አመራር ቦርድ፡፡

በእስከዳር አስማረ

ዶክተር ኃይለየሱስ ጌታሁን በ1962 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የተወለዱ ሲሆን፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን

በአዲስ አበባ ራስ ሥዩም ትምህርት ቤት ተከታትለዋል::

ሰባተኛ ክፍል ሲደርሱ ሚያዝያ 23 በመባል ወደ ሚታወቀው ትምህርት ቤት ተዛውረዋል:: ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በእንጦጦ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ትምህርታቸውን ተምረው በ1995 ዓ.ም. የመጀመርያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል::

በሕክምና ሙያ እንደተመረቁ በሰሜን ምዕራብ በሚገኝ በገጠራማው የኢትዮጵያ ክልል በሜዲካል ኦፊሰርነት ሥራቸውን የጀመሩት ዶክተር ኃይለየሱስ በሚሠሩበት አካባቢ የሚገጥማቸውን የተለያየ ችግር ተቋቁመው በአካባቢውም የሚሰጡትን የሕክምና አገልግሎት በተጨማሪ በኤች አይቪና በቲቢ በሽታዎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን ሲሠሩ ቆይተዋል:: የነበሩበት አካባቢ ገጠር ከመሆኑ የተነሳ የተሟላ የኤሌክትሪክ ኃይል ያልነበረበትና በበቂ ግንኙነት ያልነበረው በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ያለፉ ቢሆንም የነበሩበትን ችግር በማለፍ ቲቢና ኤች አይ ቪ ኤድስ ተያያዥ በሆኑ በሽታዎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን ሲሠሩ ቆይተዋል::

ዶክተር ኃይለኢየሱስ ባሳለፍነው ዓርብ ፈረንሳይ ውስጥ በተዘጋጀው 42ኛው ዩኒየን ወርልድ ኮንፈረንስ (Union World Conference) ላይ በቲቢና በኤች አይ ቪ ኤድስ በተጠቁ ሰዎች ላይ በሚከሰተው የቲቢ

ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙት ተመራማሪበሽታ ላይ ለሠሩት ሥራ የዩኒየኑ ሳይንሳዊ ሽልማት ተሸላሚ ሆነዋል::

በዓለም የጤና ድርጅት ‹‹የቲቢ ይቁም›› ክፍል አስተባባሪ የሆኑት የ41 ዓመቱ ዶክተር ኃይለየሱስ በፈረንሳይ በምትገኘው ሊል ከተማ ላይ በተደረገው የሽልማት ሥነሥርዓት ላይ ሽልማቱን በተቀበሉበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ ለሥራቸው መሳካትና ለተሸላሚነት እንዲበቁ ለተደረገላቸው ቀና ትብብር አብረው ይሠሩ ለነበሩና ለአሁን የሙያ አጋገሮቻቸው በአጠቃላይ ከሥራው ጋር ተዛማጅነት ኖሮአቸው አብረው ለሠሩ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል:: ከዚህም በተጨማሪ ለሥራቸው ተነሳሽነት እንዲኖራቸውና በትጋት የመሥራት ፍላጎት እንዲያድርባቸው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉላቸው ሁሉ ምስጋናቸውን በድጋሚ ገልጸዋል::

የዓለም የጤና ድርጅት የቲቢ ይቁም ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር ማርዬ ራቪሊዮን በሥነሥርዓቱ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት፣ ለተሸላሚው ዶክተር ኃይለየሱስም ሆነ ባስተባባሪነት ለሚመሩት ወይንም ቲቢ ይቁም ለሚባለው ክፍላቸው ትልቅ ክብርና ስኬት መሆኑ አብራርተዋል::

ጠንካራ የአመራር ብርታታቸውንና ከዘርፉ አካላት ጋር ተባብረው በመሥራታቸው ለሽልማቱ እንዳበቃቸው አክለው ገልጸዋል::

ይህ የዩኒየን ሳይንሳዊ ሽልማት (Union Scientific Prize) በየዓመቱ የሚሰጥ ሽልማት ሲሆን በቲቢና በሳንባ ጤና ላይ ጥናት በማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለሚያደርጉ ግለሰቦች የሚሰጥ ሽልማት ነው::

ዶክተር ኃይለየሱስ ከዚህ ቀደም ብሎ በአገሪቱ የመጀመርያ የሆነውን ለወጣት ሐኪሞች የሚሰጠውን ‹‹Young Public Health Award›› ተሸላሚ ናቸው::ዶክተር ኃይለየሱስ ሽልማታቸውን ከዳይሬክተሩ ዶክተር ኒልስ ቢሎ ተቀብለዋል

Page 31: Reporter Issue 1201

|ገጽ 31 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

ሩቅዓላሚው

ከከፍ ሬ ና ፍ ር

በታደሰ ገብረማርያም

የሃያ ስምንቱ ዓመቱ ሃብቶም ኃይሌ ከአንድ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ባለፈው ዓመት መጨረሻ ላይ በኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ በመጀመርያ ዲግሪ ተመርቋል:: በአሁኑ ጊዜ የኤች 2 የኮምፒውተር እና ቋንቋ ትምህርት ቤት

መሥራችና ባለቤት ነው:: ሃብቶምን ያገኘሁትና ያነጋገርኩት መገናኛ አካባቢ ካለው የቤተል ታወር ሕንጻ ሦስተኛ ፎቅ ላይ ካቋቋመው ትምህርት ቤቱ በአንደኛው ክፍል ተቀምጦ ነው::

ከመቀመጤ ‹‹አየህ! ከሚያስጠላኝ ነገር ሁሉ ተቀጣሪ ሆኖ መሥራትን ነው›› አለኝ:: ወጣቱ በተመረቀ በአጭር ጊዜያት ውስጥ እዚህ ደረጃ ላይ ሊደርስ የቻለው ተአምር በመሥራት ሳይሆን ገና ከጧቱ ዓላማ ኖሮት በመንቀሳቀሱ ነው:: ትምህርቱን በመከታተል ላይ እያለ ካነገበው ከዚሁ ዓላማ ፎቀቅ ለሚያደርገው እንቅስቃሴና ክስተት ፊት አልሰጠም:: አልተንበረከከምም::

ትርፍ ጊዜውን በአልባሌ ሥፍራ ከማሳለፍ ይልቅ መጻሕፍትን በማንበብ እንደሚዝናና፣ ይህም ሁኔታ የማንበብ ዝንባሌ አሳድሮበታል:: ለሰውነት ጥንካሬ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በእጅጉ ወሳኝ እንደሆነ ሁሉ ለአእምሮ መበልጸግም መጻሕፍትን አዘውትሮ ማንበብ ወሳኝ መሆኑንና ወጣቱም ይህንኑ ፈለግ ተከትሎ ቢሄድ ውጤታማ ሊሆን ይችላል የሚል አመለካከት አለው::

‹‹ካሰቡበት ለመድረስ ትልቁን ሚና የሚጫወተው የገንዘብ አቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማ

ነው:: ዓላማ ካለ ገንዘብና ሌሎች አስፈላጊ ነገሮች ይገኛሉ:: ይህ አይነቱም ሁኔታ ወደ ሥራ ፈጣሪነት ያመራል::››

የኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ የመጨረሻ ዓመት ተማሪ በነበረበት ወቅት ከተቀጣሪነት መውጣት አለብኝ

በሚል መንፈስ፣ ወደፊት ለሚያቋቁመው ትምህርት ቤት ፕሮጄክት ፕሮፖዛል ማዘጋጀቱን፣ በተለያዩ የኮምፒውተር ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች እየተዘዋወረ በመጎብኘት ልምድና ተሞክሮ መቅሰሙን ከማውሳት አልተቆጠበም::

ወጣቱ እንዳመለከተው፣ ከተመረቀ በኋላ ያሰበውን ዓላማ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል እንቅስቃሴ ቀጠለ:: በዚህም እንቅስቃሴ ይረዱኛል ብሎ ያሰባቸውንና ተስፋ የጣለባቸውን ወገኖች በግል ማነጋገርና ድጋፋቸውን እንዲቸሩት ሁሉን አቀፍ ጥረት አድርጓል:: ጥረቱም ተሳክቶ ፍሬ አፈራ:: እዚህ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ከረዱት ወገኖች መካከል ቤተሰቦቹ አብላጫውን ድርሻ ይይዛሉ::

‹‹ብዙዎቹ ወጣቶች እንዳየኋቸውና ጓደኞቼም እንደነገሩኝ ብዙ ጊዜ ሥራ በማፈላለግ ውድ ጊዜያቸውን ያጠፋሉ:: ይህ ደግሞ እኔን ትንሽ ያመኝ ነበር፤›› ያለው ሃብቶም የወጣቱ ሥራ ፈጣሪ መሆን አገሪቱ ለተያያዘችው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ስኬታማነት የበኩሉን አስተዋጽኦ ያደርጋል የሚል እምነት አለው::

‹‹ትምህርት ቤቱ ከተቋቋመ ገና ሦስት ወሩ ነው:: ለጊዜው የጀመርኩት በ100ሺ ብር ካፒታል ነው:: ተማሪ በብዛት መምጣት ሲጀምር ከክፍያ በተገኘው ገንዘብ አስፈላጊ የሆኑ ልዩ ልዩ የመገልገያ ዕቃዎችን አሟላሁ:: በአሁኑ ወቅት ወደ 500 የሚጠጉ ተማሪዎች አሉኝ:: በየወሩ ከ500 እስከ 4ሺ ብር ደመወዝ የሚከፍላቸው 40 መምህራንና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች አሉኝ፤›› ሲል መልሷል::

ትምህርቱ ቤቱ ጉዳዩ ከሚመለከተው መንግሥታዊ አካል ሕጋዊ እውቅና ማግኘቱን፣ በተለያዩ የትምህርት መጻሕፍት የተደራጀ ቤተመጻሕፍት እንዳለውና ከኮምፒውተር ሥልጠና እና ከእንግሊዝኛ ትምህርት ባሻገር ፈረንሳይኛ፣ አረብኛ፣ ጀርመንኛ፣ ስፓኒሽና ቱርኪስ ቋንቋዎች በተደራቢ እንደሚሰጥ ተናግሯል::

ሕጋዊ እውቅና ሊያገኝ የቻለውም የማስተማሪያ መሳሪያዎቹ ዘመናዊና፣ የተሟሉ መሆናቸውንና የመማሪያ ክፍሎቹ ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ መዘጋጀታቸውን በመረጋገጡ እንዲሁም የቤተ መጻሕፍቱ እና የመምህራኑ ስብጥር እና ይዘት፣ የመማር ማስተማር ሥራ በሚገባ ከተፈተሸና ከተገመገመ በኋላ መሆኑን ከወጣቱ ማብራርያ ለመረዳት ተችሏል::

በአዲስ አበባ ተጨማሪ፣ በተለያዩ ከተሞች አንዳንድ ት/ቤት የመከፍተት ራዕይ እንዳው አስረድቷል:: ሃብቶም ኃይሌ

‹‹ከፊታችን የሚጠብቀን ዓብይ ጉዳይ የሊቢያን

ሰላም ማስፈንና መረጋጋትን ማንገሥ ቢሆንም፣ ከሁሉም በላይ ግን ሰብዓዊ መብትን ማስከበር ቀዳሚው አጀንዳችን

ይሆናል፤››

ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልራሂም አል ኪብ፣

ባለፈው ሰኞ ምሽት የሊቢያ ብሔራዊ የሽግግር መንግሥት

ባካሄደው ምርጫ ከተሰየሙ በኋላ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ::

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያየኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት አነስተኛ የቁጠባና ብድር አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ሲሆን ከዚህ በታች ባሉ ክፍት የሥራ መደቦች መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ ብልጫ ውጤት ያመጡትን በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል፡፡

ተ.ቁ. የሥራ መደቡ መጠሪያ ብዛት የሥራ ቦታ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃና የሥራ ልምድ ደረጃ ደመወዝ ምርመራ

1 ጠቅላላ ሂሳብ ኃላፊ 1 ሀዋሳ ዋናው መ/ቤት በአካውንቲንግ ቢኤ ዲግሪ እና 6 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ያለው/ላት

XIV በተቋሙ የደመወዝ ስኬል መሠረት

በድጋሚ የወጣ

2 ጥናትና ዶክሜንተሽን ኦፊሰር 4 ሀዋሳ ዋናው መ/ቤት በኢኮኖሚክስ፣ በማኔጅመንት፣ ስታስቲክስ እና በተመሳሳይ የትምህርት መስክ ኤም ኤ ዲግሪና 4 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ወይም ቢኤ ዲግሪና 6 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ያለው/ላት

XIV በተቋሙ የደመወዝ ስኬል መሠረት

በድጋሚ የወጣ

3 ጁኒየር የህግ ባለሙያ 2 ሶዶ፣ ሆሳዕና እና ሚዛን ቅ/ጽ/ቤቶች

በህግ አድቫንስ ዲፕሎማና 4 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ወይም የኮሌጅ ዲፕሎማና 6 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ያለው/ላት

X በተቋሙ የደመወዝ ስኬል መሠረት

በድጋሚ የወጣ

4 ፕላንና ፕሮጀክት ዝግጅትና ትንተና ኦፊሰር

2 ሀዋሳ ዋናው መ/ቤት በኢኮኖሚክስ፣ በማኔጅመንት፣ ስታስቲክስ እና በተመሳሳይ የትምህርት መስክ ኤም ኤ ዲግሪና 4 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ወይም ቢኤ ዲግሪና 6 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ያለው/ላት

XIV በተቋሙ የደመወዝ ስኬል መሠረት

5 ሲኒየር ኦፕሬሽን ኦፊሰር 2 ሀዋሳ ዋናው መ/ቤት በኢኮኖሚክስ፣ በማርኬቲንግ፣ በማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ የትምህርት መስክ ኤም ኤ ዲግሪና 4 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ወይም ቢኤ ዲግሪና 6 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ያለው/ላት

XIV በተቋሙ የደመወዝ ስኬል መሠረት

6 ሲኒየር ዳታቤዝ አድሚኒስትሬተር

1 ሀዋሳ ዋናው መ/ቤት በኮምፒውተር ሳይንስ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም፣ በኢንፎርማቲክስ፣ በኢንፎርሜሽን ሲስተም፣ በስታትስቲክስ እና በተመሳሳይ የትምህርት መስክ ቢኤስሲ ዲግሪና 4 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ያለው/ላት

በስምምነት

7 ዳታቤዝ አድሚኒስትሬተር 1 ሀዋሳ ዋናው መ/ቤት በኮምፒውተር ሳይንስ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም፣ በኢንፎርማቲክስ፣ በኢንፎርሜሽን ሲስተም፣ በስታትስቲክስ እና በተመሳሳይ የትምህርት መስክ ቢኤስሲ ዲግሪና 3 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ያለው/ላት

- በስምምነት

8 ሲኒየር ኔትወርክ አድሚኒስትሬተር

1 ሀዋሳ ዋናው መ/ቤት በኮምፒውተር ሳይንስ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም፣ በኢንፎርማቲክስ፣ በኢንፎርሜሽን ሲስተም፣ በስታትስቲክስ እና በተመሳሳይ የትምህርት መስክ ቢኤስሲ ዲግሪና 4 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ያለው/ላት

- በስምምነት

ማሳሰቢያ፡- • የምዝገባ ቦታ፡- ዋናው መ/ቤት የሰው ሀብት ሥራ አመራርና ልማት መምሪያ ቢሮ ቁጥር 19• የምዝገባ ጊዜ፡- ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት • አመልካቾች የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃችሁን ዋናውንና ኮፒውን በመያዝ በአካል ወይም በፖ.ሳ.ቁ. 353 ወይም በኢሜል አድራሻ Email: [email protected] ወይም በፋክስ ቁጥር

046-220-20-52/046-220-81-25 በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ • ለሁሉም ክፍት የሥራ መደቦች ተመዝጋቢዎች ከታወቀ ዩኒቨርስቲ/ኮሌጅ የተመረቁ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡• ከላይ ከተገለጸው የትምህርትና የሥራ ልምድ በላይ ያላቸው መወዳደር ይችላሉ፡፡

ተቋሙ!

Page 32: Reporter Issue 1201

ገጽ 32|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

ይማሩ! ዓለምን ያናግሩ!ዓለማችን አንD mNdR በሆነበT zmN åNå {N lmìR ¶Lwsኑ ከÒn g^z_W auƒN nW:: ለነጋዴ ች ፣ ለMuƒ™N ¤ ltìÞ { ¤ ltm™ìÞ {¤ lë^ፕÉìÄ{¤ bGBrs³Y DRJቶች ለሚሰሩና በአረብ ሀገራት መስራት ለሚፈልጉ በልዩ ሁኔ¬ የተሰናዳ የቋንቋ ዎ‹ ስልጠና ተዘጋጅቷል::

• I퓃ን በልዩ ሁኔታ እናስተምራለን::

Ly„ yì@¶dRgN • mMU™Ñê{N bé°N ¤ bë&²Y³ bl_É{ yaˆÅ° ug™T btm±±Y

SLe³ yse&³ yt±·®[W kmÒ³[WM b®Y yåNåW ugR tw®Ð{ mÒ³[W

• yTMURT as½½{N zm³§#³ GL: mÒn& • åNåWN baXR g^z_ ANë^³gݳ ANë^smƒ bሚ¶S{L t†Kn@K ìStìR

mê®{N • ARΔ yì@m{ T g^z_ l¼M M[> mÒn&

• åNå[WN Bê ±YÒN ²U®[WNM XMR ìstìR mê®{N¥¥

* ³_¨<ኑ ይመዝገቡና ዓለምን ያናግ\!

ለበለጠ መረጃስልክ +251 115 509 809 ፋክስ +251 115 509 722

አድራሻ፡- ካዛንቺስ ኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል አጠገብ ንግስት ታወር 2ኛ ፎቅ (201)Email:[email protected]

www.ihacs.org

የኤስያ ቋንቋዎች• ዐረብኛ• ቻይንኛ (ማንዳሪን)• ጃፓንኛ• ህንድኛ• ኮሪያኛ

የአውሮፓ ቋንቋዎች• እንግሊዝኛ• ፈረንሳይኛ• ስፓኒሽ• ፖርቹጊስ

1. Job Title: Manager - Customer Service I

Educational Qualification and Work Experience:- Bachelor Degree in Accounting, Accounting

& Finance, Banking & Finance, Management, Economics or business related field and 2 years of experience as Customer Relationship Officer or Senior Customer Service Officer or Branch Controller

orDiploma in Accounting, Management, Economics or business related field with 5 years of experience as customer Relationship Officer or Senior customer Service officer or Branch Controller

Required Competencies and Specification o Ability to work in teamo Ability to manage works without supervisiono Demonstration of strong personal commitment to learn

particular skill o Good interpersonal skills i.e. courtesy for customers and

good communication skillo Acting with integrity o Flexible and adapt to new business needo Knowledge of basic computer applicationso Conflict management skillo Certified in the banking applications softwareo Good knowledge of bank accounting o Knowledge of basic service marketing techniques

Job Location :- Mizan Teferi, Gambela, Gimbi, Dembidolo, Humera, Woldia, Logia, Chiro, Asela, Hosana, Debretabor, Enjibara , Debre Birhan and Gilgel Beles

2. Job Title: Branch Manager I

Educational Qualification and Work Experience:- Bachelor Degree in Accounting, Accounting &

Finance, Banking and Finance, Management, Economics or business related field and 3 years of experience in Banking Operation

orDiploma in Accounting, Management, Economics or business related field with 6 years of experience in banking operation

Required Competencies and Specification

o Strong ability to communicate clearly both orally and in writingo Well organized and efficiento Good interpersonal skillso Ability to lead and coach others o Take initiative and set prioritieso Ability to realize the ongoing Business Process Reengineering activityo Acting with integrityo Flexible and adapt to new business needso Computer literateo Good knowledge of bank accounting o Knowledge in service marketing

Job Location :- Dembi Dolo , Gilgel Beles and GambelaFor All Job Positions:-

Term of Employment:- Permanent Salary :- Attractive

Application Procedure

Interested and qualified applicants are invited to submit their Application, Curriculum Vitae, copy and Originals of Credentials and Documents related to education and work experience to Construction & Business Bank – Human Resource Management Process at our Head Office 6th floor located in front of Addis Ababa University Collage of Commerce.

Tel:- 0115-15 55 05, 0115 15 27 25, 0115 52 38 49 Fax :- 011 5 51 -22 -73Closing Date of Application: Within 5 (Five) Working Days after the announcement.

ኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ አ.ማConstruCtion & Business Bank s.C

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

ተልካም ኃ/የተ/የግ/ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ አመልካቾች አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

የሥራ መደቡ ፋይናንስና አስተዳደር

የትምህርት ደረጃ በፋይናንስና አስተዳደር እውቅና ካለው ኮሌጅ በዲግሪ የተመረቀ/ች የሥራ ልምድ ቢያንስ 8 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሥራ ልምድ ያለው/

ያላት በፒችትሪ አካውንቲንግና ሌሎች የኮምፒውተር ፕሮግራሞችን በሚገባ መሥራት የሚችል/የምትችል

ፆታ አይለይምየቅጥር ሁኔታ በቋሚነት ደመወዝ በስምምነት የሥራ ቦታ አዲስ አበባ ብዛት 1 (አንድ)አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ቀናት ውስጥ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃችሁን ኦሪጅናል እና ፎቶ ኮፒውን በመያዝ ድርጅታችን በሚገኝበት ደብረ ዘይት መንገድ አቃቂ ቃሊቲ ማሰልጠኛን አለፍ ብሎ ከውሃ ልማት ፊት ለፊት ማመልከት ይችላሉ፡፡

ቴልካም ኃ/የተ/የግ/ማህበርፖስታ ሣ.ቁ. 42434

ስልክ ቂጥር 011-4-39-65-16ፋክስ 011-4-66-99-87

Page 33: Reporter Issue 1201

|ገጽ 33 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

ል ና ገ ር

በግርማ ሰይፉ ማሩ

ሪፖርተር በእሑድ ጥቅምት 19 ቀን 2003 ዓ.ም. ዕትም የቆይታ አምድ፣ ከከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር ዴኤታ ከሆኑት አቶ ደሳለኝ አምባው ጋር አዲስ በወጣው የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 721/2003 አስመልክቶ ያደረገውን ቃለ ምልልስ አስነብቦናል:: በቃል ምልልሱ የተካተቱትን አንዳንድ ነጥቦች አንስቼ ሐሳቤን ብቻ ላካፍላችሁ:: እነርሱም፡-

• በረቂቁ ላይ ሕዝብ ተወያይቶበታል፤

• ምክር ቤቱ ቀደም ሲል በተለያዩ መድረኮች በረቂቅ አዋጁና በፖሊሲው ዙርያ ውይይት እንደተደረገበት ታሳቢ በማድረግ ነው አዋጁን ያፀደቀው፤

• ንብረቱም ቤት ከሆነ ወዲያውኑ ወደ ሊዝ ውስጥ ይገባል፤ እና

• ...... ከዚህ በኋላ ገዢው በአካባቢው የሊዝ ዋጋ መሠረት ክፍያ ይጀምራሉ፤

የሚሉት ናቸው::

እነዚህን የባለሥልጣኑን አስተያየት ስሰማ ዝም ማለት ተገቢ አይደለም በሚል አስተያየቴን መሰንዘር ተገቢ ነው

ብዬ ወሰንኩ:: በቅድሚያ በረቂቁ ላይ ሕዝብ ተወያይቶበታል ብለው በድፍረት የገለጹትን ሊገፉበት ባለመፈለግ ‹‹በበቂ ባይሆንም፣ ሰፊ ባይሆንም፣›› ወዘተ በማለት ለመንሸራተት ሞክረዋል:: ትክክለኛው መልስ መሆን ያለበት ግን ሕዝብ አልተወያየበትም የሚል ነው:: ሕዝብ ለሚለው የከተማ አስተዳደር ሠራተኞች/ካድሬዎች ያደረጉትን ስብሰባ ወይም በቢሮ የተደረጉትን አውደ ጥናቶች ከሆነ ልዩነታችን ሕዝብ በሚለው ትርጉም ላይ ይመስለኛል:: ስለዚህ ሕዝብ ማለት ለእርስዎ ማን ነው?

በተለይ በቃለ ምልልሱ ይህ ጉዳይ ‹‹የመሬት ጉዳይ ነው ሁሉንም ሰው ይነካል›› የሚል ሐሳብ ይዘው በድፍረት ባይገፉበትም ሕዝብ ተወያይቶበታል ለማለት መሞከር ተገቢ አይደለም:: ሕዝብ ቀርቶ ሕዝብ ወክሎናል በምክር ቤት ወንበር ይዘናል እያልን ያለን ተወካዮች በቅጡ ክርክር ማድረግ ሳይሆን፣ አንብቦ ለመምጣት የሚያስችል ጊዜ በተለመደው

አሠራር እንኳን አላገኘንም:: ስለዚህ ሕዝብ በቀጥታ ብቻ ሳይሆን፣ በውክልና እንኳን በቅጡ ለመወያየት ዕድል አላገኘም:: ስለዚህ ሕዝቡ አልተወያየበትም::

ምክር ቤቱ ቀደም ሲል በተለያዩ መድረኮች በረቂቅ አዋጁና በፖሊሲው ዙርያ ውይይት እንደተደረገበት ታሳቢ በማድረግ ነው አዋጁን ያፀደቀው ያሉትም ከእውነታው ውጭ ነው:: ምክር ቤቱ ይህንን አላለም:: በምክር ቤቱ የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር እንኳን ያሉት፣ ‹‹አጣዳፊ ስለሆነ፣

ይህ አዋጅ ለትራንስፎርሜሽኑ ዕቅዱ መሳካት ካለው ጠቀሜታ አንፃር፣ መንግሥት በጥልቀት ያየው በመሆኑ፣›› ወዘተ የሚል ማብራሪያ ነው የሰጡት::

ይልቁንም አፈ ጉባዔው በመዝጊያ ንግግራቸው አጣዳፊ ከመሆኑ አንፃር እንጂ ቋሚ ኮሚቴ አይቶት፣ የሕዝብ አስተያየት ተሰብሰቦ ቢሆን ጥቅም እንጂ ጉዳት እንደሌለው ገልጸው ነበር:: ነበር ምን ዋጋ አለው እንጂ:: ለምን አጣዳፊ እንደሆነ ግን አሁንም ግልጽ አይደለም:: የሕዝብ ድምፅ ጠቃሚ ቢሆንም የተፈራበት ምክንያት ወደፊት ይገባን ይሆናል የተደበቀው ሚስጢር ሲገለጥ::

ይህ አዋጅ የዜጎችን መብቶች የሚጥስ ነው የሚል አስተያየት እየተደመጠ ባለበት ሁኔታ፣ ሚኒስትር ዴታው ይባስ ብለው አዋጁ ላይ ያልተገለጸ ጉድ ጨመሩበት:: ከጉዶቹ አንዱ ‹‹ንብረቱ ቤት ከሆነ ወዲያውኑ ወደ ሊዝ ይገባል›› የሚለው ነው:: አዋጁ የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ እንጂ ስለቤት የወጣ ነገር የለውም:: ይህንን በተመለከተ ማብራሪያ ቢሰጡን እንወዳለን:: በዚህ ላይ ከዚህ በላይ ማለት ተገቢ አይመስለኝም::

ሌላው ‹‹ . . . ሽያጭ ከተካሄደ በኋላ ገዢው በአካባቢው የሊዝ ዋጋ መሠረት ክፍያ ይጀምራል፤›› የሚለው ነው:: ይህንን ከአዋጁ ከየትኛው አንቀጽ ላይ እንዳመጡት ግልጽ አይደለም:: በቢሮ ውይይት ሲደረግ ተነስቶ ከሆነ ግን የዜጎችን ንብረት ለመውረስ ከጀርባ እየተዶለተ ነው ማለት ነው የሚያስብል ነው::

አዋጁ ላይ ነባር ይዞታን በሚመለከት አንቀጽ 5(1) ‹‹ነባር ይዞታዎች ወዲ ሊዝ ሥሪት የሚቀየሩበት ሁኔታ ሚኒስትሩ በሚያቀርበው ዝርዝር ጥናት ተመሥርቶ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ይወሰናል፤›› ነው የሚለው:: ይህ አንቀጽ ይዋል ይደር እንጂ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ የመወረስ ስጋት ይፈጥራል ነበር የነበረን አስተያየት፤ ስጋት ሆኖ የነበረውም ይህ ነው::

በእኔ አመለካከት ነባር ይዞታ ያላቸው ዜጎች ከዛሬ ጀምሮ ይህ ቦታ ለ99 ዓመት ወይም ለ20 ዓመት ወይም ሌላ ቁጥር ተጠርቶ ይዞታችሁ የሚፀናው ለዚህ ያህል የሊዝ ዘመን ነው ይባላሉ የሚል ነው:: ባለነባር ይዞታዎች በሽያጭ ሲያስተላልፉም በሊዝ ዘመን ለተፈቀደላቸው ዓመት ብቻ ስለሚሆን መብታቸውን ያጠብባቸዋል የሚል ነበር:: ይህ በራሱ በነባር ይዞታዎች የቦታ ዝውውር ላይ ጫና በመፍጠር ኢኮኖሚው ላይ መቀዛቀዝ ይፈጥራል የሚል ነበር ስጋታችን::

አሁን ክቡር ሚኒስትር የገለጹልን ግን ከዚህ የዘለለ ነው:: ‘የነባር ባለይዞታ ይዞታውን በሽያጭ ሲያዛውር ገዢው በቀጥታ ወደ ሊዝ ሥሪት ይገባል በሚለው መሠረት ገዢው የይዞታ ሰርተፊኬት ሲሰጠው የሊዝ ዘመኑ ለመኖሪያ፣ ለድርጅት፣ ወዘተ ተብሎ በተመለከተው መሠረት ተደርጎ ይሰጠዋል’

የሚለውን በተሳሳተ ሁኔታ በመተርጎም ገና ከሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ሳይወጣ፣ ከአዋጁ መንፈስ ውጭ ገዥው በአካባቢው የሊዝ ዋጋ መሠረት ክፍያ ይጀምራል አሉን::

በንግድና በኢንቨስትመንት ሥራ ላይ ለመሠማራት የሚወስኑ ሰዎች ይህንን ዓይነት ጉዳይ በቅጡ ገምግመው አውጥተውና አውርደው ስለሚወስኑ፣ አሁን ያስተላለፉት መልዕክት ነባር ይዞታዎችን ከንብረታቸው ለማፈናቀል ካልሆነ በስተቀር አንድም እርባና ያለው የኢኮኖሚ ጥቅምም ሆነ አገራዊ ፋይዳ አይኖረውም::

ነገሩ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ አጥንቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት በማቅረብ ስለሚል ይህ መልስ የጥናቱ ፍንጭ ሊሆን ይችላል:: የእኛን አገር ጥናቶች ባለፉት ጊዜያት በደንብ አይተናል (የሪል ስቴት አልሚዎችን፣ የዋጋ ተመንን፣ ወዘተ):: የዘንድሮ አዋጅ ግን ይህንን አይልም ክቡር ሚኒስትር::

የአዋጁ አንቀጽ 5(3) ‹‹. . . ከውርስ በስተቀር በማናቸውም መንገድ ለሌላ ሰው ከተላለፈ ንብረቱ የተላለፈለት ሰው የቦታ ባለይዞታ ሊሆን የሚችለው በሊዝ ሥሪት መሠረት ይሆናል፤›› ሲል በምንም ዓይነት መንግሥት በተጨማሪ የሊዝ ገንዘብ ይሰበሰባል ማለት አይደለም:: ከላይ ለማስረዳት እንደሞከርኩት ነባር ይዞታው የተላለፈለት ሰው በነባር ይዞታነት አይቀጥልም፤ ወደ ሊዝ ሥሪት ይገባል:: ይህም የመጠቀሚያ የጊዜ ገደብ ይበጅለታል ማለት ነው እንጂ፣ ተጨማሪ ክፍያ ይኖርበታል የሚል አይደለም:: ይህ ቀደም ሲል በነበረውም የሊዝ አዋጅ የነበረ ነው::

ስለሆነም ክቡር ሚኒስትር ከአዋጁ መንፈስ ውጭ በሚሰጡት አስተያየት ብዙ ጉዳት እንደሚከተል ማሰብ ተገቢ ይመስለናል:: የሚወጣው መመርያ ይህ መንፈስ ነው ያለው እያሉን ከሆነ ባለነባር ይዞታዎች በግልጽ እንዲያውቁት ተደርጎ እርማቸውን እንዲያወጡ መምከር ነው:: በነገራችን ላይ ከኢኮኖሚም ሆነ ከፖለቲካ መብቶቻችን በተናጠል እየተገፋን ስንሄድ ምን አገባን የምንል ብዙ ስለሆንን፣ የሌሎች ጥቃት ካልተሰማን ነግ በእኔ መሆኑን ማስታወስ ተገቢ ጭምር ይመስለኛል::

አንድ ነገር አክዬ ለመጨረስ በዚህ አዋጅ ተጎጂ የሚሆኑት ከኢሕአዴግ በፊት በምሪት ቦታ የያዙት ዜጎች ናቸው:: ይበልጥ ግን የሚጎዱት በደርግ ትርፍ ቤትና መሬት ተወርሶበቸው፣ ነገር ግን ከዛሬ ነገ የተሻለ ቀን ይመጣል ለተወረሰ ንብረት ካሳ ይከፈለናል ይቅርታም እንጠየቃለን ብለው ሲጠብቁ ቀሪው ቦታቸውንም ሊወረሱ መሆኑን የሚሰሙት ኢትዮጵያዊያን ናቸው:: ይህ እንግዲህ ሕገ መንግሥቱ ያጎናጸፋቸው ፀጋ መሆኑ ነው መሬት የመንግሥትና የሕዝብ ብቻ ነው::

ከአዘጋጁ፡- አቶ ግርማ ሰይፉ ማሩ ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ናቸው::

ክቡር ሚኒስትር አዋጁ እንዲህ ይላል እንዴ?

ይህ አዋጅ የዜጎችን መብቶች የሚጥስ ነው የሚል አስተያየት እየተደመጠ ባለበት ሁኔታ፣ ሚኒስትር ዴታው ይባስ ብለው አዋጁ ላይ ያልተገለጸ ጉድ ጨመሩበት:: ከጉዶቹ አንዱ ‹‹ንብረቱ ቤት ከሆነ ወዲያውኑ ወደ ሊዝ ይገባል›› የሚለው ነው:: አዋጁ የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ እንጂ ስለቤት የወጣ ነገር የለውም:: ይህንን በተመለከተ ማብራሪያ ቢሰጡን እንወዳለን:: በዚህ ላይ ከዚህ በላይ ማለት ተገቢ አይመስለኝም::

‹‹የመሬት ኢንቨስትመንቱ... ከገጽ 27 የዞረ

ምናልባት የጋዜጠኞች ወይም የሌሎች ጉዳይ ነው:: ሁኔታው ግን አለ:: የመሬት ሽሚያ የሚለውን ቃል እኔ አልወደውም:: ለምን ቢባል ገና ቁምነገሩ ላይ ሳንነጋገር ወደ ፀብ ስለሚያመራን ነው:: ነገሩን በደንብ እንየውና እንመርምረው:: እየተካሄደ ያለውን እንወቀው በሚል መነሻ እኔ ‹‹የመሬት ኢንቨስትመንት›› ማለቱን መርጫለሁ:: የመሬት ሽሚያ ከተባለም የማየው ነው:: አዝማሚያው በብዛት የውጭ ኢንቨስትመንት ላይ ነው:: ከአንዱ በስተቀር የኢትዮጵያ ኢንቨስተሮች በንፅፅር ሁለት ወይም ሦስት ሺሕ ሔክታር ነው የሚያገኙት:: ጥቂቶች አምስት ሺሕ የያዙ አለ:: ዳያስፖራውም እንደዚያው ነው:: የኢንቨስትመንት ፕሮግራሙ በግልጽ አይናገረውም እንጂ አዝማሚያው የውጭ ኢንቨስትመንትና ኢንቨስተሮች ላይ ቀልቡ ያረፈ ነው:: መንግሥትም የውጭ ኢንቨስተሮች የተሻለ ካፒታል፣ የተሻለ ቴክኖሎጂ፣ የተሻለ የእርሻ ዘዴ አላቸው እያለ ነው:: ካፒታል ሊኖራቸው ይችላል:: ካሩቱሪ ትልቅ ከባንያ ነው:: የተሻለ የእርሻ ዘዴ አላቸው የሚለው ለእኔ ያጠራጥረኛል::

ሪፖርተር፡- መንግሥት ለውጭ ባለሃብቶች ያደላው የቴክኖሎጂ ሽግግር አገኛለሁ በማለት ነው:: እርስዎ መስክ ሔደው ባካሄዱት ጥናት እነዚህ የሚባሉት ነገሮች እውነት ይታያሉ?

አቶ ደሳለኝ፡- ቴክኖሎጂ ከየት ወዴት እንደሚሸጋገር ግልጽ አይደለም:: መንግሥት ይህንን ግልጽ ሊያደርግ ይገባዋል:: ከኢንቨስተሩ ወደ አነስተኛ ገበሬዎች ይሻገራል ማለት ቀልድ ይመስለኛል:: ኢንቨስተሩ በትልልቅ ማሽን ቢሠራ አንድ ሔክታር ወይም ግማሽ ሔክታር ላይ የሚያርሰው ገበሬ ያንን ተሞክሮ ይወስዳል መባሉ ለእኔ አይታየኝም::

ሪፖርተር፡- ስለዚህ ግብርና ላይ ምንም የቴክኖሎጂ ሽግግር አይኖርም ማለት ነው?

አቶ ደሳለኝ፡- እኔ ምንም የቴክኖሎጂ ሽግግር የለም ባይነኝ:: በጥናቱም ያስቀመጥኩት እርሱን ነው:: ለምን ቢባል አነስተኛ መሬት ላይ የሚጣጣረው ገበሬ ከእነዚያ ግዙፍ ኩባንያዎች የሚወስደው ነገር መኖሩ አይታየኝም:: የእርሻዎቹ ዓይነት የሚጠይቁት ቴክኖሎጂ የተለያየ ነው:: ሰፋፊ እርሻዎችና ትናንሾቹ የሚመጣጠኑበት ምንም ነገር የለም:: የአገር ውስጥ የግብርና ምሁራን እንደነ ካሩቱሪ ያሉት እዚህ መጥተው የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ በሚገባ ሳያውቁ ዘለው ወደ እርሻ መግባታቸውን እየተቹ ነው:: ገበሬው በሚያየውና ባለው ዕውቀቱ መሠረት እነዚህ ኩባንያዎች የሚሠሩትን እያየ እየሳቀባቸው እኰ ነው:: የእርሻ ዘዴያቸው ከገበሬው የሚሻል ሆኖ አልተገኘም:: ምርታማነታቸውን ወደፊት ለማሳደግ አግሮ ኬሚካል በሰፊው እየረጩ የሚጠቀሙ ይመስለኛል:: ይኼ ደግሞ አካባቢ ላይ የሚያመጣው ችግር ግልጽ ነው::

ሪፖርተር፡- በጥቅሉ ለእርሻ ዘርፍ ትልልቆቹ ኢንቨስትመንቶች

የሚያመጡት የቴክኖሎጂ ልውውጥና ሽግግር የለም ብሎ መደምደም ይቻላል ማለት ነው?

አቶ ደሳለኝ፡- እኔ እንደሚገባኝ አዎ:: ሪፖርተር፡- ከጥናትዎ አኳያ መሬት ለውጭ ባለሃብቶች መሰጠቱ

የሚያመጣውን ተፅዕኖ ነጥብ በነጥብ ቃኝተዋል:: ጠቅለል ባለ ሁኔታ የሚያመጡትን ጉዳት ቢገልጹልን?

አቶ ደሳለኝ፡- የሚያሳስቡ ነገሮች አሉ:: የውጭ ኢንቨስተሮች ካፒታሊስት ናቸው:: ትርፍ ነው የሚፈልጉት:: በተቻለ መጠን ቶሎ ትርፍ ማግኘት ይፈልጋሉ:: ስለዚህ አካባቢ ይጉዳ አይጉዳ ጥያቄ ውስጥ መግባት የሚፈልጉ አይመስለኝም:: ይኼ ትልቅ ጉዳት ይፈጥርብናል:: ሌላው ትልቅ ትኩረት ያስፈልገዋል የምለው ኢንቨስትመንቱ ሲሰጣቸው የሚያመርቱትን ወደ ውጭ መላኩ ላይ ያተኰረ ስለሆነ የአገሪቱን የምግብ ዋስትና የሚመለከትና የሚፈታ አይሆንም:: ወደ ውጭም እንዲላክ የፋይናንስና ሌላም ማበረታቻ ይሰጠዋል:: መንግሥት የሚፈልገው ወደ ውጭ መላኩን ነው:: የውጭ ምንዛሪ አገኛለሁ በሚል ተስፋ:: ስለዚህ ይኼንን ሁሉ መሬት ይዞ ምርቱን ወደ ውጭ መላክ የአገሪቱን የምግብ ዋስትና ችግር የሚያባብስ ነው:: የምግብ ዋስትና ችግር እርግጥ ይህ መንግሥት የፈጠረው አይደለም:: ቀድሞ የነበረ ነው:: የሺሕ ዓመት ታሪክ ብናይ ይኼ አገር በምግብ ራሱን እንዳልቻለ እንረዳለን:: ይህ ባለበት ሁኔታ ለምን ኢንቨስትመንቱ ከምግብ ዋስትና ጋር መያያዝ እንዳልቻለ አሳሳቢ ነው:: ለጊዜው እነዚህ እርሻዎች ቀጥታ ለምግብ ዋስትናው ችግር አስተዋፅኦ ባያደርጉም ውሎ አድሮ አስተዋጽኦ ማድረጋቸው አይቀርም:: የሥነ ምኅዳር ችግሩ እንዳለ ሆኖ ነው እንግዲህ:: በተለይ ኦሮሚያ ውስጥ የሚሰጡ መሬቶች የግጦሽ መሬቶች ናቸው:: ስለዚህ የአካባቢና የምግብ ዋስትናን ችግሮች ያባብሳሉ::

ሪፖርተር፡- ጥናቱ ለሚመለከታቸው መሥሪያ ቤቶች ቀርቧል ተብሎ ይገመታልና ምላሻቸው ምን ይመስላል?

አቶ ደሳለኝ፡- ጥናቱን ወስደን ባንሰጣቸውም የውይይት መድረክ አካሂደናል:: ጥናቱም ለሕዝብ ይፋ ሆኗል:: ተበትኗል:: ባለሥልጣኖቹ ግን ያዩትም አይመስለኝም::

ሪፖርተር፡- ወደኋላ ልመልስዎትና አንዳንድ በመሬት አሰጣጥ ላይ የሚወጡ የመንግሥት መረጃዎች እርስ በርስ የሚጣረሱ ናቸው:: ክልሎች የሚሉትና የፌዴራሉ የሚናገረው ይለያያል:: ይህንን መስክ ሄዳችሁ እንዳጣራችሁ መገመት ይቻላል? እንደዚህ ያለውስ አሠራር ምን ዓይነት ስጋት ያመጣል?

አቶ ደሳለኝ፡ መሬት መስጠት የተጀመረው ይህ መንግሥት ሥልጣን በያዘ በሦስተኛና በአራተኛው ዓመት ገደማ ነው:: ኢትዮጵያውያን ግለሰቦች ለኢኮኖሚው ጥቅም በማለት መሬት ጠይቀው በየክልሉ መስጠት ከተጀመረ ቆይቷል:: ያንን ክልሎች ነበሩ የሚያከናውኑት:: እነኚህ መሬቶች ትንንሾች ናቸው::

ግፋ ቢል 200፣ 500፣ አልፎ አልፎ ሁለት ሺሕ ሔክታር የተሰጣቸው በርካቶች ናቸው:: የመረጃ ቋቱን ተመልክተን ያረጋገጥነው ከወሰዱት አብዛኞቹ አልተጠቀሙበትም:: አንዳንድ ቦታ እንዲያውም መሬቱ ላይ የነበረውን ዛፍ ጨፍጭፈው ከሸጡ በኋላ እጃቸውን አጣምረው ቁጭ ያሉ አሉ:: እስካሁን ድረስ በቤንሻንጉል ይህ ነገር እየተከሰተ ሰዎችን ወደ ፍርድ ቤት ለማቅረብ እያሰቡ ናቸው:: ሁኔታዎች የተቀየሩት የዓለም የምግብ ቀውስ ሲመጣ ነው:: በተለይ ከ1998 ዓ.ም በኋላ ማለት ነው:: ኢንቨስተሮች በተለይ የእስያዎቹ ህንድና ቻይና የምግብ ችግራቸውን ለመቅረፍ መሬት ባላቸው አገሮች ተከራይተን አምርተን ወደ አገራችን እንውሰድ ብለው ተነስተዋል:: አፍሪካን መዳረሻ አድርገዋል:: በተለይ የመካከለኛው ምሥራቆቹ የእርሻ መሬት ስለሌላቸው ይህንን መንገድ ይመርጣሉ:: ብዙ ገንዘብ ቢኖራቸውም ገንዘብ አይበላም:: በዓለም ገበያ ውስጥ በቀውሱ ምክንያት ምግብ ጠፍቷል:: ብዙ ቢሊዮን ዶላር ይዘህ ብትዞር ምግብ የሚሸጥልህ የለም:: ወደ አፍሪካ ያመጣቸው ይኼ ነው:: ይኼንን ነገር በኢትዮጵያ ብቻ መገደብ የለባችሁም:: አፍሪካ በሙሉ ነው:: ታንዛኒያ፣ ሱዳን፣ በትንሹም ቢሆን ኬንያ፣ ሞዛምቢክ፣ አንጎላን ጨምሮ 22 የአፍሪካ አገሮች እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የመሬት ኢንቨስትመንት እያሉ እየሰጡ ናቸው:: የውጭ አገሮች ለምግብ ዋስትናቸው ሲሉ መምጣታቸው ነው የእኛንም መንግሥት መጠቀም አለብኝ ከሚል ስሜት የከተተው:: የመሬት ኢንቨስትመንት ፕሮግራሙን ሰፋ አድርጎ ያወጣው ያን ጊዜ ነው:: ከዚህ በፊት የያዙት እንዳሉ ናቸው:: አንዳንዶቹ እየተወሰደባቸው ነው:: በተለይ እ.ኤ.አ በ2002 የኢንቨስትመንቱ ሕግ ሲመጣና ለጋሽነቱን ሲያሳይ ብዙ ኢንቨስተሮች ለመምጣት አበረታታቸው:: የአፍሪካ ኅብረት ጉዳዩ አሳስቦት ውይይቶችን ማድረግ እየጀመረ ነው:: በመሬት ኢንቨስትመንት ላይ አሳሳቢ ጉዳዮች እየተከሱ በመሆኑ አንድ ወጥ ፖሊሲ እንዲኖር እንቅስቃሴዎች እየተካሄዱ ናቸው::

ሪፖርተር፡- ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች ጋር ሲነፃፀር የእኛ አሳሳቢነቱ ምን ያህል ነው? በጣም የተጋለጠ ስጋት ጋርጦብናል?

አቶ ደሳለኝ፡- ተመሳሳይ ነው:: ሁሉም ጋ የሚታየው አንድ አይነት አካሄድ ነው::

ሪፖርተር፡- ጥናቱ እንደ መፍትሔ የሚያቀርባቸው አንኳር ነጥቦች ምንድን ናቸው?

አቶ ደሳለኝ፡- ነገሩ አሳሳቢ የሆነው መንግሥት ከመነሻው ከሕዝቡ ጋር ውይይት አለማድረጉ ነው:: መንግሥት አጋጣሚውን ለመጠቀም በችኮላ የገባበት ነው:: አንዳንድ ክልሎች ኢንቨስተሩ በጻፈው ደብዳቤ ብቻ መሬት ሲሰጡም ነበር:: ወደኋላው ላይ በትንሹም ቢሆን መልክ እንዲይዝና አካሄድ እንዲኖረው እየተደረገ ነው:: አንድ አካባቢ ላይ መንግሥት ራሱ ለእርሻ የሚሆን 50 ሚሊዮን ሔክታር መሬት አለኝ ብሎ ነበር:: ቆየና ደግሞ 10 ሚሊዮን አለኝ ብሎ ጽፏል:: አሁን አሁን መልክ ለማስያዝ እየተሞከረ ነው:: ሆኖም በቅርብ የወጣው መመርያም ሙሉ ለሙሉ ሥራ ላይ አልዋለም:: ስለዚህ ትልቁ

ነገር የሕዝብ ውይይት ሊደረግበት የሚገባ ይመስለኛል:: በርካታ ባለሙያዎች፣ ገበሬው ጭምር ሐሳብ ይስጡበት:: ሌላው መሬት የመንግሥት በመሆኑ መንግሥት መስጠት ስለሚችል በየአካባቢው ያሉትን የግብርና ባለሙያዎች ሳያማክሩ ነው የሚገቡበት:: ውይይትም አልተደረገም:: ምክክር ያስፈልጋል:: ሌላው ጥንቃቄ ሊደረግበት ይገባል:: የውጭ ኢንቨስትመንት አይኑር የሚል ሰው አይደለሁም:: ነገር ግን የሚሰጠን ጥቅም በደንብ ታይቶ፣ የሚሰጥበት አካባቢ ያሉ ሰዎችንም አማክሮና ተወያይቶ ቢደረግ፣ ጥቅም የመጋራት ሥርዓት ቢኖረው የተሻለ ነው እላለሁ:: ጥቅም መጋራት በዓለም ደረጃ በቅርብ የወጣ አሠራር ነው:: የማዕድን ፍለጋ ላይ የሚሠሩ ኩባንያዎች ዱሮ እንደልባቸው ማዕድኑን አውጥተው መሸጥ ነበር ሥራቸው:: አሁን ግን አንዳንድ አካባቢ የሚደረገው ኩባንያው ካገኘው ትርፍ 20 በመቶ ወይም ከዚያ በላይ መልሶ ማዕድኑን ወዳገኘበት አካባቢ ኢንቨስት እንዲያደርግ ነው:: ይኼን ዓይነት አመላካከት ቢኖር ጥሩ ነበር:: ጋምቤላ ላይ አንድ ኢንቨስተር ገብቶ፣ ሠርቶ ከትርፉ ይህንን ያህል እዚያው ኢንቨስት አድርግ ቢባል ጥሩ ነበር:: ሌላው ጥንቃቄና አስፈላጊ ቁጥጥር በአካባቢ ተፅዕኖ ላይ ሲደረግ አይታይም:: ይህንን ቁጥጥር የሚያደርጉት በክልል ያሉ የአካባቢ ጥበቃ ቢሮዎች ናቸው:: ቁጥጥር ለማድረግ አቅሙም፣ ሙያውም በበቂ የላቸውም:: እነሱ ይኼን አድርግ ያንን አታድርግ ብለው ኢንቨስተሩን ለመቋቋም አቅም የላቸውም:: እነዚህ አካላት አቅም ካገኙ በኋላ ነበር ቢያንስ ኢንቨስትመንቱ መካሄድ የነበረበት:: ያ ገና አልሆነም:: አሁንም ደግሜ የምናገረው የመሬት ኢንቨስትመንቱ የዚህችን አገር የምግብ ዋስትና አያረጋግጥም ነው:: ይኼ ያሳስባል::

ሪፖርተር፡- አሁንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚከራከሩበትን ነጥብ ላንሳ:: የተሰጠው መሬት ካለው ያልተነካ መሬት አኳያ የመሬት ሽሚያ አሳሳቢ አይደለም ብለዋል:: አሁን ካለው መሬት ምን ያህሉ እንደተሰጠ ጥናትዎ ሊያየው ሞክሯል?

አቶ ደሳለኝ፡- አስቸጋሪ ነው:: ካለን ከጠቅላላው መሬት አይደለም የተሰጠው:: ምንም ዓይነት ጉዳት ሳያደርስ ለግብርና የሚውል መሬት ምን ያህል ነው? ከዚህ ውስጥ ገበሬው የማይጠቀምበት ምን ያህል አለ ነው ጥያቄው:: እንጂ በጠቅላላው ምን ያህል መሬት አለ አይደለም:: ሊታረስ የሚችልና ከታረሰ የአካባቢ ጉዳት ሊያመጣ የማይችል ምን ያህሉ ነው እንጂ መነጋጋሪያው የአገሩቱ ጂኦግራፊያዊ ስፋትማ ትልቅ ነው:: በእኔ ግምት በእነኚህ መስፈርቶች ስንነሳ ሊኖር የሚችለው መሬት በጣም ትንሽ ነው:: መሬት ብዙ ስላለን እንሰጣለን የሚባለው ነገር ትክክል አይደለም ባይ ነኝ:: ባዶ መሬት ስላለ ብቻ ጥቅም ላይ አልዋለም፤ ለውጭ መሰጠት አለበት ማለት አይቻልም:: ከጥቅም አኳያ ሲታይም ገበሬው የሚያርሰው፣ ለግጦሽ የሚፈልገው፣ ለቤት መሥሪያና ለማገዶ፣ ለውኃ ምንጭነት የሚፈልገው መሬት ስላለ ገበሬው ያልያዘው፣ ያልተጠቀመበት የሚባለው አገላለጽ ትክክል አይደለም:: ገበሬው የሚያርሳት አንድ ሔክታር መሬት ብቻ ተይዛ፣ ይህች ነች የገበሬው መሬት ሌላው ባዶ ነው ማለት ትክክል አይደለም::

Page 34: Reporter Issue 1201

ገጽ 34|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

ለአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበርት ምክር ቤትአባላት በሙሉ

ውድ አባላት፤አዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት 7ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ታህሣሥ 5 ቀን 2004 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡30 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ያካሂዳል፡፡ ጉባዔው ምክር ቤቱን ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት የሚመሩ የቦርድ አባላት የሚመረጡበት ጭምር ስለሆነ ልዩ አጋጣሚ የሚፈጥር ነው፡፡

የዲሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም፣ ምክር ቤታችንን በቅርብ የሚያቁና ለሥራው ጊዜያቸውን መስዋዕት ለማድረግ ፈቃደኛ የሆኑ አባላት የሚገኙበት ኮሚቴ ተቋቁሞ ጥቆማዎቹን ለመቀበል ዝግጁ ሆኗል፡፡

ስለዚህ የምክር ቤታችን አባላት በኢ-ሜል በተላከላችሁ መስፈርት መሠረት ከአባላት መካከል ብቻ ለፕሬዝዳንትነት እና ለቦርድ አባልነት ዕጩዎችን እንድትጠቁሙ ምክር ቤቱ ጥሪውን ያቀረባል፡፡ ስለሆነም በአባሪነት ተያይዞ በኢ-ሜል የተላከላችሁን የዕጩዎች መጠቆሚያ ቅጽ ሞልታችሁ ለአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ፣ በሚል አድራሻ በኤንቨሎፕ በማሸግ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2004 ዓ.ም. ሜክሲኮ አደባባይ ለሚገኘው የምክር ቤቱ ጽ/ቤት በአካል በመምጣት ወይም በመላክ የጥቆማ ቅጹ እንዲደርሰን እንድታደርጉ የዘወትር ትብብራችሁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

አዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበርት ምክር ቤት

Vacancy AnnouncementRosetta General Business Plc is engaged in import export Air transport service, Manufacturing, Real estate and serves as a holding company of many local and foreign business entities.

Rosetta would like to invite qualified applicants to apply for the following vacant position:-

Position: Finance Manager Qualification: BA Degree in Accounting from a recognized University. Experience: Minimum 8 years relevant experience out of which at least 5 years in Supervisory position Others: Knowledge of Peachtree is mandatory

Good communication skill and team spirit Work Place: Addis Ababa Term of employment Permanent Salary: Competitive Required Person: One

All interested and qualified applicants should submit their CV and copies of non returnable credentials to the head office (near Bole high school) in person or through the following address within 10 (ten) working days from the date of this announcement .

Address:Rosetta Generale Business PLC Administration Department Tel: 0116-18-37-65/75 P.O.Box 80854 Addis Ababa

Page 35: Reporter Issue 1201

|ገጽ 35 | ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

www.ethiopianreporter.com

ስ ፖ ር ት

በሔኖክ ያሬድ

ጌርማን ሲልቫ በ1986 ዓ.ም. የኒውዮርክ ማራቶንን ለመጀመርያ ጊዜ አሸንፎ አገሩ ሲገባ የሜክሲኮ መንግሥት የጠየቀው ምን ልሸልምህ ብሎ ነበር:: ሹማምነቱንም እባካችሁ ለትውልድ መንደሬ የኤሌክትሪክ መብራት አስገቡልኝ አላቸው ከወር ቆይታ በኋላ ቴኮሜት ብርሃን አገኘች::

ከሦስት ዓመት በኋላም ከኒውዮርክ ሩጫው በኋላ በጎ አድራጎትን ማከናወን ርዕዩ አደረገው፤ በሜክሲኮ ከተማ መኪናዬን እያሽከረከርሁ ስዘልቅ በርካታ ደሀ ልጆችን ተመለከትኩ የ13 ወይም 14 ዕድሜ ባላቸው ሴቶች ልጆች የወለዱም ያረገዙም ይገኙባቸዋል:: እነዚህን ልጆች መርዳት አለብኝ ብዬ ወሰንኩ:: ብሎ ቃሉን የሰጠው ለአሶሲየትድ ፕሬስ ዘጋቢ ነበር::

የ1986 እና 87 ዓ.ም. የኒውዮርክ ማራቶን አሸናፊው የሲልቫ ሠናይ ተግባር በዚህ ብቻ የተወሰነ አይደለም:: ልጆች ሯጮች እንደሆኑ የተለያዩ የሩጫ ውድድሮችን በማዘጋጀት ብቻ ሳይወሰን የመሮጫ ጫማም ትጥቅን በመስጠት ያበረታታ ነበር::

ሁለገብ ሠናይ ተግባሩን የተረዳው የኒውዮርክ የጎዳና ሩጫ ውድድር አዘጋጁ ‹‹ኒውዮርክ ሮድ

ራነርስ›› የ2011 (2004 ዓ.ም.) የአበበ ቢቂላን ዓመታዊ ሽልማት እንዲቀዳጅ አድርጎታል::

ሽልማቱ የኦሊምፒክ ማራቶን የሮምና ቶኪዮ ሻምፒዮኑ በኩር (ሌጀንደሪ) አበበ ቢቂላ የተሰየመ ነው:: በ1970 ዓ.ም. በኒውዮርክ የተጀመረው ‹‹የአበበ ቢቂላ ሽልማት›› (Abebe Bikila Award) በመም (ትራክ) እና ጎዳና ላይ ለሚካሄደው የረዥም ርቀት ሩጫ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሚሰጥ ነው:: የአምናው ተሸላሚ የኬንያው ፖል ቴርጋት ሲሆን ከኢትዮጵያ ብቸኛው ተሸላሚ በ1974 ዓ.ም. ክብሩን የተቀዳጀው ሻምበል ማሞ ወልዴ ነው::

ሲልቫ የዘንድሮውን የአበበ ቢቂላ ሽልማት ክብር ማግኘቱን በኒውዮርክ ሮድ ረነርስ ፕሬዚዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሜሪ ዊተንበርግ የተበሰረው ሻምበል አበበ ቢቂላ ባረፈበት ዕለት ጥቅምት 15 ቀን 2004 ዓ.ም. ነው::

የመጀመርያው ጥቁር አፍሪካዊ የኦሊምፒክ ማራቶን ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የነበረው አበበ ቢቂላ በሮም (ጳጉሜን 5 ቀን 1952 ዓ.ም.) በባዶ እግሩ፣ በቶኪዮ ደግሞ (ጥቅምት 11 ቀን 1957 ዓ.ም.) በጫማው በተከታታይ በማሸነፍ ሁለት ወርቅ መሸለሙ ይታወሳል::

በ1961 ዓ.ም. በደረሰበት የመኪና አደጋ ሳቢያ

ለአካል ጉዳት የተዳረገው አበበ ቢቂላ ጥቅምት 15 ቀን 1966 ዓ.ም. በ41 ዓመቱ ማረፉ ይታወቃል::

ኒውዮርክ በሽልማቷ በየዓመቱ አበበ ቢቂላን ትዘክራለች:: አዲስ አበባስ? በመዲናችንና በአዳማ በአበበ ቢቂላ የተሰየሙ ስታዲዮሞች ቢኖሩም ከዚያ ባለፈ ለአበበ ቢቂላ ምን አከናወንን? የሴኔጋሏ መዲና ዳካር ወደ ብሔራዊ ስታዲዮሟ የሚያስገባውን መንገድ በ1971 ዓ.ም. ባዘጋጀችው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና አጋጣሚ ‹‹አበበ ቢቂላ መንገድ›› ማለቷም ይዘከራል::

ነገር በነገር ቢወሳ አይደንቅምና በዘንድሮው የኒውዮርክ የአበበ ቢቂላ ሽልማት አጋጣሚ አበበ ቢቂላን በቀለም አበባ ስንዘክረው፣ የሚከተሉትን አንኳር ጉዳዮች በማንሣት ነው:: ከ12 ዓመት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘውን ፒኮክ መናፈሻ ወደ ኢትዮ-ጃፓን መናፈሻ በመለወጥ ለአበበ ቢቂላ የመታሰቢያ ሐውልት እንደሚቆምለት ተነግሮ የነበረው ሁኔታ ከምን ደርሶ ይሆን?

በቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ ስፖርትና ኦሊምፒክ መሪዎች ዘመን፣ ለአበበ ቢቂላ መዘከሪያ፣ ለድሎቹ መታወሻ ይሆን ዘንድ በአዲስ አበባ ስታዲዮም ምዕራባዊ በር 11 ቁጥር መግቢያ አጠገብ የተተከሉት ምስሎቹስ የት ደረሱ?

የአበበ ቢቂላን ሽልማት ያገኘው ሲልቫየአበበ ቢቂላ ሐውልት ከምን ደርሶ ይሆን?

የ2004 ዓ.ም. ተሸላሚው ጌርማን ሲልቫ የ1974 ዓ.ም. ተሸላሚው ማሞ ወልዴ ከአበበ ቢቂላ ጋር

በደረጀ ጠገናው

በተያዘው የውድድር ዓመት አገሪቱን በአፍሪካ የኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የሚወክለውን ቡድን ለመለየት የክለቦች ጥሎ ማለፍ ዋንጫ የፍጻሜ ግማሽ ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲዮም ይካሔዳል::

መታሰቢያነቱ ለቀድሞ የቅዱስ ጊዮርጊስና ብሔራዊ ቡድን ተጨዋች ለነበረው ኢንስትራክተር መንግሥቱ ወርቁ የሆነው የዘንድሮው የኢትዮጵያ ክለቦች ጥሎ ማለፍ ዋንጫ፣ ቀደም ሲል በ11 የፕሪምየር ሊግ ክለቦች መካከል እንደሚደረግ ፕሮግራም ተይዞለት የነበረ ቢሆንም፣ ነገር ግን የደደቢት እግር ኳስ ክለብ ሊሳተፍ ባለመቻሉ በ10 ክለቦች መካከል ሊከናወን ግድ ብሎታል::

ለዋንጫው የሚያልፉትን ሁለት ቡድኖች ለመለየት በ10 ሰዓት ሙገር ሲሚንቶ ከመብራት ኃየል፣ በ12 ሰዓት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሐረር ቢራ በአዲስ አበባ ስታዲዮም ዛሬ ይጫወታሉ::

ባለፉት ሁለት ዓመታት በፕሪምየር ሊጉ ላለመውረድ ሲጫወት የቆየው መብራት ኃይል፣ በዚህ ዓመት በአዲስ አበባ ዋንጫም ሆነ በጥሎ ማለፍ ጨዋታ የሚጠቀስ እንቅስቃሴ ካሳዩት ክለቦች አንዱ ለመሆን በቅቷል:: ቡድኑ ሰሞኑን እንደሚያሳየው አቋም ከሆነ ለሙገር ሲሚንቶ ቀላል እንደማይሆን እየተነገረለት ይገኛል::

ቡልጋሪያዊው አሠልጣኝ ዮርዳን ስቶይኮቭ የተጨዋቾቻቸውን አቅም በመለየቱ በኩል የሚስተዋልባቸውን ክፍተት ማረምና ማስተካከል ከቻሉ ቡድናቸውን በጥሎ ማለፍ ብቻ ሳይሆን፣ በፕሪምየር ሊጉ ጭምር ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ::

ምሽት 12 ሰዓት ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስና ሐረር ቢራ የሚያደርጉት ጨዋታ እንደመጀመርያው ሁሉ እንዲጠበቅ ከሚያደርገው ምክንያቶች፣ ባለፉት ዓመታት በአፍሪካ መድረክ በተደጋጋሚ አገሪቱን በመወከል የሚታወቀው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከለመደው ተሳትፎ ላለመውጣት የሚጫወት መሆኑ ነው::

ጠንካራ በረኛና ተከላካይ ክፍል እንዳለው የሚነገርለት ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ በተለይም በረኛው ሮበርት የቋሚ በረኛነትን ዕድል ከያዘ ካለፈው ግማሽ ዓመት ጀምሮ ግብ አልተቆጠረበትም:: ሆኖም ግን ቅዱስ ጊዮርጊስ የተጋጣሚ ቡድንን ተከላካይ ማስጨነቅ የሚችል የፊት መስመር ተጨዋች ችግር እንዳለበት የሚናገሩ አሉ:: ምክንያቱም የሚሉት እነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች ቡድኑ ተጋጣሚዎቹን እያሸነፈ የመጣው በጠባብ የግብ ልዩነት መሆኑን በማስረጃነት ይጠቅሳሉ::

በደረጀ ጠገናው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ2014 ለሚደረገው የዓለም ዋንጫ፣ የማጣርያ ማጣርያውን ቅዳሜ ኅዳር 2 ቀን 2004 ዓ.ም. ጅቡቲ ላይ ከሶማሊያ ጋር ይጫወታል:: የመልሱን ጨዋታ ደግሞ ኅዳር 17 ቀን 2004 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲዮም እንደሚያከናውን የኢትዮጵያን እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል::

የአገሪቱ እግር ኳስ ከአፍሪካ ዋንጫ ከራቀ ሦስት አስርት ዓመታትን አስቆጥሯል:: ይህንን አስከፊ የእግር ኳስ ታሪክ ለመቀየር፣ ፌዴሬሽኑን በተለያዩ አጋጣሚዎች የመምራት ዕድሉን ያገኙ ሰዎች የተለያዩ አውሮፓውያን አሠልጣኞችን በማስመጣት ጥረት ቢያደርጉም ሊሳካ ግን አልቻለም::

ችግሩ ምን እንደሆነ ማወቅ የሚያስችል ጥናታዊ ጽሑፍ በተደጋጋሚ ቀርቧል፣ ነገር ግን መፍትሔ ሊሆን አልቻለም:: ብሔራዊ ቡድኑን ለማሠልጠን በተለያየ ጊዜና ወቅት ወደ አገሪቱ የመጡ የውጭ አሠልጣኞች፣ ‹‹ኢትዮጵያውያን በተሰጥዖ የተካኑ›› ስለመሆናቸው የሚናገሩት ብስራት ሁሉ ዓመት እንኳ ሳይሞላው የስንብታቸው ዜና ሲሰማ ቆይቷል፤ አሁንም ቀጥሏል:: አሠልጣኞቹ እንዴትና በምን መስፈርት መጡ? የሚለው በግልፅ ሳይታወቅ ስንብቱም በተመሳሳይ ይከናወናል:: ወሬውም ከአንድ ሳምንት ሳያልፍ ይቀርና እንደገና ወደ ሌላ ስህተትና ውድቀት መሄድ በኢትዮጵያ እግር ኳስ የተለመደ መሆን ብቻ ሳይሆን፣ ቀልድም እየሆነ ይገኛል::

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጋቦንና ኢኳቶሪያል ጊኒ በጋራ ከሚያዘጋጁት የአፍሪካ ዋንጫ ውጭ ቢሆንም፣ እንደገና ብራዚል በ2014 ለምታዘጋጀው የዓለም ዋንጫ የማጣርያ ምድብ ድልድል ጨዋታ ይጠብቀዋል:: ከዚያ በፊት ግን በእግር ኳስ አቅማቸው ደካማ የሆኑ እንደ ኢትዮጵያና ሶማሊያ የመሳሰሉ አገሮች ወደ ምድብ ድልድሉ ለመግባት የቅድመ ማጣርያ ጨዋታዎችን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል::

‹‹ዕድሉ ከተሰጠኝ ለሚቀጥለው የአፍሪካ ዋንጫ ብቁ ብሔራዊ

ቡድን ማዘጋጀት እችላለሁ፤›› ሲሉ የነበሩትና ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ላለፉት አምስት ወር ቆይታ የነበራቸው ቤልጅየማዊው አሠልጣኝ ቶም ሴንት ፊዬት በአሁኑ ወቅት ለዕረፍት በሚል ወደ አገራቸው በሔዱበት ስንብታቸው ተሰምቷል:: ስለሆነም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ያለ አሠልጣኝ መሆኑን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሠልጣኝ ለመቅጠር ማስታወቂያ አውጥቷል:: የዚህ ዕድል ተጠቃሚዎች እነማን ይሆኑ? የሚለው በአሁኑ ወቅት ባይታወቅም፣ ከአንዳንድ ምንጮች ለመረዳት እንደተቻለው ባለፉት ዓመታት በየመን ሊግ ቆይታ የነበራቸው አሠልጣኝ ሥዩም ከበደ በፌዴሬሽኑ የታሰቡ ስለመሆኑም ተሰምቷል:: አሠልጣኙ በየመን እየተከናወነ ባለው የፖለቲካ አለመግባባት ወደ አገራቸው ከመጡበት ዕለት ጀምሮ አንዳንድ የፕሪምየር ሊግ ክለቦች እያነጋገሯቸው ነው:: ከእነዚህ ክለቦች መከላከያ አንዱ መሆኑ ሲነገር ቆይቷል::

ሥዩም ከበደ ለብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝነት መታጨቱ ተሰማ

የጥሎ ማለፉ ፍጻሜ ግማሽ ዛሬ ይካሔዳል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያደርገውን ዓመታዊ የማራቶን ውድድር ጥቅምት 26 ቀን 2004 ዓ.ም. እንደሚያከናውን አስታወቀ::

ፌዴሬሽኑ ከሞሐ ለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማኅበር ጋር በመተባበር በሚያከናውነው ዓመታዊ ማራቶን፣ ታዋቂ የክለብና የግል ተወዳዳሪዎች ለ16ኛ ጊዜ እንደሚያሳትፍ ፌዴሬሽኑ የላከው መግለጫ አስረድቷል::

የአዲስ አበባ ሞሐ ማራቶን እሑድ ይካሔዳል

ለዋንጫው የሚያልፉትን ሁለት ቡድኖች ለመለየት በ10 ሰዓት ሙገር ሲሚንቶ ከመብራት ኃየል፣ በ12 ሰዓት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሐረር ቢራ በአዲስ አበባ

ስታዲዮም ዛሬ ይጫወታሉ::

Page 36: Reporter Issue 1201

ገጽ 36|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ጥቅምት 22 ቀን 2004

የዲዛይንና ዝግጅት በሚዲያ ኮምዩኒኬሽን ሴንተር አሳታሚ የሚዲያና ኮምዩኒኬሽን ሴንተር አታሚ፡ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ክ/ከተማ፡ አራዳ ቀበሌ፡ 17 የቤት ቁጥር፡ 984

ወደ ገጽ ዞሯል5

በኃይሌ ሙሉ

በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አመራር አባላት መካከል የተፈጠረው ውዝግብ መቋጫ ባለማግኘቱ፣ የፓርቲው የወደፊት ዕጣ ፈንታ አደጋ ላይ ወድቋል:: አብዛኛዎቹ የፓርቲው ጽሕፈት ቤቶች በገንዘብ እጥረት ምክንያት ተዘግተዋል::

ላለፈው አንድ ዓመት ያህል እርስ በርስ ሲበጣበጡ የቆዩት የመኢአድ ሥራ አስፈጻሚ አባላት አለመግባባታቸውን በውይይት መፍታት ባለመቻላቸው ምክንያት፣ ሥራ አስፈጻሚው ለሁለት ተከፍሏል:: ይህንን ተከትሎም ጥቅምት 12 ቀን 2004 ዓ.ም. አስቸኳይ ስብሰባ ያካሄደው የመኢአድ የአዲስ አበባ ምክር ቤት፣ ኢንጂነር ኃይሉ ሻውል በሚመሩት ቡድን ላይ ተቃውሞውን ሰንዝሯል:: በፓርቲው ውስጥ የተጠራቀሙ ችግሮችን ለመፍታትም አስቸኳይ የማዕከላዊ ምክር ቤት ስብሰባ መጠራት እንዳለበት አስገንዝቧል::

መስከረም 14 ቀን 2004 ዓ.ም. በተካሄደ ምርጫ በአዲስ መልክ የተመሠረተውና ኢንጂነር ኃይሉ ከሚመሩት የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ዕውቅና ያላገኘው የአዲስ አበባ ምክር ቤት ለሪፖርተር በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ በፓርቲው ማዕከላዊና ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መካከል አለመግባባት የተፈጠረው የአመራሩ ምርጫና ምደባ ከመነሻው በአባላት ግምገማና በዴሞክራሲያዊ አግባብ ባለመከናወኑ ነው::

‹‹በአብላጫ ድምፅ የሚፀድቅ ሐሳብ ዴሞክራሲያዊ አሠራርና የሠለጠነ አካሄድ በመሆኑ፣ በማዕከላዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አብላጫ ድምፅ የሚወሰነውን ሐሳብ ከልብ እንደግፋለን፤›› የሚለው ምክር ቤቱ፣ በማዕከላዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የተፈጠረውን አለመግባባት በሠለጠነና በዴሞክራሲያዊ ውይይት መፍታት ሲቻል፣ ሰበብ እየተፈለገ አባላትን ማገድ ተቀባይነት የሌለው ድርጊት በመሆኑ እንደሚቃወመው አስታውቋል::

ከአሥራ ስምንቱ የመኢአድ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት መካከል አሥሩ ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጡት መግለጫ፣ የፓርቲውን ዋና ጸሐፊ ከአመራርነት ማገዳቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በኢንጂነር ኃይሉ የሚመራውና ስምንት አባላት ያሉት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በበኩሉ፣ አንጃ ፈጥረዋል ያላቸውን እነኚህን

የአመራር አባላት ከሥራ ማገዱን ከትናንት በስቲያ አስታውቋል::

የመኢአድ ዋና ጸሐፊ አቶ ተስፋዬ ታሪኩ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ሰባቱ የሥራ አስፈጻሚ አባላት ሰሞኑን የታገዱት የፓርቲውን ሕገ ደንብ የሚጥስ ተግባር በመፈጸማቸውና አንጃ በመፍጠራቸው ነው:: ሌሎቹ ሁለቱ የሥራ አስፈጻሚ አባላት ቀደም ብለው በፈጸሙት ሕገወጥ ድርጊት መታገዳቸውን፣ አንደኛው ደግሞ ባስገቡት የሥራ መልቀቂያ መሠረት ጥያቄያቸው ተቀባይነት ማግኘቱን ዋና ጸሐፊው ይገልጻሉ::

መስከረም 14 ቀን 2002 ዓ.ም. በተካሄደው የአዲስ አበባ መኢአድ ምክር ቤት ምርጫ ሥራ አስፈጻሚው

ያላመነበትና ያልተወከለበት በመሆኑ፣ በሥራ አስፈጻሚው ዕውቅና ያልተሰጠው መሆኑን የገለጹት አቶ ተስፋዬ፣ ፕሬዚዳንቱ ኢንጂነር ኃይሉ ባለፈው እሑድ የፓርቲውን አባላትና ደጋፊዎች ባነጋገሩበት ወቅት ማብራሪያ ተሰጥቶበት መግባባት ላይ መደረሱን ተናግረዋል::

የአዲስ አበባ ብሔራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፍቃዱ በልሁ ግን የሚሉት ሌላ ነው:: ከዚህ በፊት የተቋቋመው የመኢአድ ምክር ቤት ጊዜያዊ ኮሚቴ በ2001 ዓ.ም. በነበረው የምርጫ ሕግ ይመራ የነበረ በመሆኑ፣ ሐምሌ 30 ቀን 2001 ዓ.ም. በፀደቀው ሕግ መሠረት አዲስ ምርጫ በማስፈለጉ ሁሉም የጠቅላላ ጉባዔ አባላት በተገኙበት የምክር ቤትና የሥራ አስፈጻሚ ምርጫ መካሄዱን የሚናገሩት መቶ አለቃ ፍቃዱ፣ ‹‹አዲስ አበባ ባሉት ቀጣናዎች የምክር ቤትንና የሥራ አስፈጻሚ አባላትን መምረጥ ይቻላል፤›› ከማለት ውጪ፣ በደንቡ ላይ ሥራ አስፈጻሚ ሳይገኝ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም የሚል ነገር ባለመኖሩ፣ ‹‹ምርጫው ሕገወጥ ነው›› የሚለው የእነኢንጂነር ኃይሉ ውንጀላ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ይገልጻሉ::

መኢአድ ውስጥ ኢንጂነር ኃይሉ የሚሾሟቸው ሰዎች ብቻ በኃላፊነት እንደሚቀመጡ የሚናገሩት መቶ አለቃ ፍቃዱ፣ የአሁኑ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ምርጫም በሥራ አስፈጻሚው ተቀባይነት ያጣው የእርሳቸው ፍላጐት ተፈጻሚ ባለመሆኑ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል::

‹‹መኢአድ ንብረትነቱ የአንድ ግለሰብ የሆነ ፋብሪካ ነው ማለት ይቻላል፤ እንደ ፓርቲ ብዙኅኑ በጋራ የሚነጋገሩበትና የሚወስኑበት አይደለም:: ብዙኀኑ የሚወስነው ውሳኔ በአንድ ሰው ይሻራል፤›› በማለት ፓርቲው ምን ያህል በአንድ ሰው ተፅዕኖ ሥር እንደወደቀ ይገልጻሉ::

በአሁኑ ወቅት በፓርቲው ውስጥ በተፈጠረው የማያባራ ብጥብጥ ምክንያት በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉት ደጋፊዎች የገንዘብ ድጋፍ መስጠት ያቆሙ መሆናቸውን የገለጹት መቶ አለቃ ፍቃዱ፣ ይህንን ተከትሎም በክልልና በአዲስ አበባ ለተከፈቱ ጽሕፈት ቤቶች የቤት ኪራይ መክፈል ባለመቻሉ

አብዛኛዎቹ ጽሕፈት ቤቶች ተዘግተዋል

መኢአድ አደጋ ላይ ነውአሥር የሥራ አስፈጻሚዎች ታግደዋል የአዲስ አበባ ምክር ቤት ፕሬዚዳንቱን ተቃውሟል

በብርቱካን ፈንታ

የአዲስ አበባ ከተማ ቆሻሻዎች ተጠራቅመው ይደፉበት ከነበረው የረጲ የቆሻሻ መጣያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ሊጀመር መሆኑ ታወቀ::

ያለማቋረጥ በሚወጣው ጭስ ሳቢያ የአካባቢውን ነዋሪዎች አማርሮ የነበረው ረጲ የቆሻሻ መጣያን መልሶ በማልማት ለአረንጓዴ ቦታነት ለመጠቀም ታስቦ በተደረገው እንቅስቃሴ፣ ከቆሻሻ ከሚገኘው የሚቴን ጋዝ አማካይነት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደሚቻል መረጋገጡን፣ የመልሶ መጠቀምና ማስወገድ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች የሥራ ሒደት መሪ አቶ መኮንን ታፈሰ ለሪፖርተር ገልጸዋል::

ሰላሳ ሁለት ሔክታር መሬት ከሚሸፍነው የረጲ ቆሻሻ መጣያ ውስጥ እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ 19 ሔክታር ያህሉ እየተደለደለ መዘጋቱን ያስታወቁት ኃላፊው፣ ቆሻሻ መጣያው ሙሉ በሙሉ ከተዘጋ በኋላ ከደረቅ ቆሻሻ የሚገኘውን እንጥፍጣፊ (ሚቴን) ጉድጓዶችን በመቆፈር እንዲጠራቀም ከተደረገ በኋላ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ሥራ ይጀመራል::

እስካሁን ባለው ሒደት ከአንድ ኪዩቢክ ሜትር ደረቅ ቆሻሻ አንድ ኪዩቢክ ሜትር ሚቴን እንደሚገኝ፣ ከዚሁም ሚቴን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደሚቻል መረጋገጡን አቶ መኮንን ገልጸዋል:: የተገኘውን የሚቴን ጋዝ በጄኔሬተር አማካይነት ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል በመለወጥ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን በሽያጭ እንደሚቀርብ አቶ መኮንን አስረድተዋል::

ሥራውን ማካሄድ ለሚችል ድርጅት በጨረታ መሰጠቱን የሚናገሩት አቶ መኮንን፣ በስፍራው በቂ ካርቦን እንዳለ በመረጋገጡ ካርቦንን የመሸጥ ዕድሉም እንዳለ አብራርተዋል::

በፕሮጀክቱ ላይ በቁፋሮና ቱቦ በመዘርጋት ላይ የተሰማራው የዳንኤል አበራ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭና የኮንስትራክሽን ዕቃዎች አቅራቢ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳንኤል አበራ እንደገለጹት፣ በዓለም ላይ ትልቁና መጥፎ ጋዝ የሚባለውና የምድርን ሙቀት የሚያዛባው ሚቴን ጋዝ ነው:: ሚቴን ጋዝ በረጲ የቆሻሻ መድፊያ ስፍራ እንደሚገኝና ከዚህ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደሚቻል አቶ ዳንኤል ገልጸዋል::

ከረጲ የቆሻሻ መጣያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ሊጀመር ነው

ኢንጂነር ኃይሉ ሻውል